Sunday, November 3, 2013

በጂጂጋ ፍተሻው ተጠናክሯልከቀኑ 10 ሰዓት በኋላ ባጃጆች አይሰሩም ከምሽቱ አራት ሰዓት በኋላ ሰዓት እላፊ ታውጇል በኢትዮጵያ ሶማሊያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከባለፈው ረቡዕ ጀምሮ እስከ ህዳር 30 ድረስ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መዘጋታቸውን ምንጮች ገለፁ፡፡ በከተማው የሚገኙ 2300 ያህል ባጃጆችም ከቀኑ አስር ሰዓት በኋላ ስራ እንዳይሰሩ መታገዳቸውን ምንጮች የገለፁ ሲሆን ከምሽቱ አራት ሰዓት በኋላም ሰዓት እላፊ ስለታወጀ በከተማው ነዋሪዎች ከአራት ሰዓት በኋላ እንደማይንቀሳቀሱ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡

ከቀኑ 10 ሰዓት በኋላ ባጃጆች አይሰሩም
ከምሽቱ አራት ሰዓት በኋላ ሰዓት እላፊ ታውጇል
በኢትዮጵያ ሶማሊያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከባለፈው ረቡዕ ጀምሮ እስከ ህዳር 30 ድረስ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መዘጋታቸውን ምንጮች ገለፁ፡፡ በከተማው የሚገኙ 2300 ያህል ባጃጆችም ከቀኑ አስር ሰዓት በኋላ ስራ እንዳይሰሩ መታገዳቸውን ምንጮች የገለፁ ሲሆን ከምሽቱ አራት ሰዓት በኋላም ሰዓት እላፊ ስለታወጀ በከተማው ነዋሪዎች ከአራት ሰዓት በኋላ እንደማይንቀሳቀሱ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡
“በምሰራበት የመንግስት መስሪያ ቤት ዋና የስራ ሂደት ባለቤት ነኝ” ያሉ አንድ ግለሰብ፤ የመንግስት ሰራተኛ ስራውን ትቶ በከተማው ካሉ ልዩ ሀይሎች ጋር በመሆን ሰዎችን ወደመፈተሽ ስራ መግባቱን ተናግረዋል። አንድ ሰው ከከተማው አንድ ቦታ ተነስቶ የሚፈልግበት እስኪደርስ ቢያንስ አምስትና ስድስት ጊዜ ሊፈተሽ ይችላል ያሉት እኒሁ የመንግስት ሠራተኛ፤ ለከተማው ፀጥታ ሲባል ፍተሻው ተገቢ ቢሆንም ለ40 ቀን የመንግስት ስራ ቆሞ ሰራተኛውን ፈታሽ ማድረግ ግን አግባብ እንዳልሆነና እንደሚቃወሙት ገልፀዋል።
በቅርቡ የሚከበረውን የብሔር ብሔረሰቦች በዓል በጅጅጋ ለማክበር የሚደረገውን ዝግጅት ተከትሎ አካባቢውን ለመጠበቅ በሚል ፍተሻው ቢጠናከርም የመንግስት ሰራተኞች ለ40 ቀን ስራ ትተው ለፍተሻ መሰማራታቸው አግባብ እንዳልሆነ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
“የብሄር ብሄረሰቦች በዓል በልዩነታችን ውስጥ አንድነታችንን የምናይበት እና የምንከባበርበት እንጂ ዜጎች ስራ አቁመው ወዳልተፈለገ ስራ የሚሰማሩበትና የሚሰቃዩበት መሆን የለበትም” ሲሉ አማረዋል፤ ግለሰቡ፡፡ “አንድ ባጃጅ ለሹፌሩን እና ለባለቤቱ ቤተሰቦች ገቢ የሚያስገኝ በመሆኑ ከ10 ሰዓት በኋላ እንዳይሰሩ መከልከሉን እንቃወማለን” ያሉት ስማቸውን ያልገለፁ ሌላው የመንግስት ሰራተኛ፤ ጉዳዩን የፌዴራል መንግስት አውቆት እልባት እንዲያገኝና የክልሉ መንግስት ስህተቱን እንዲያርም አሳስበዋል፡፡
“እኔ የመንግስት ሰራተኛ ባለመሆኔ የመንግስት መስሪያ ቤት ስለመዘጋቱ የማውቀው የለም” ያሉት አንዲት የከተማዋ ነዋሪ፤ ባጃጆች ከአስር ሰዓት በኋላ ስራ እንደማይሰሩና ሰዓት እላፊ መታወጁን ግን እንደሚያውቁ ተናግረዋል፡፡ “በአጋጣሚ መታወቂያ ሳትይዢ ከቤት ከወጣሽ ታፍሰሽ ወደ እስር ቤት ትወሰጃለሽ” ያሉት ሌላው ነዋሪ፤ ያለፖሊስ ማዘዣ ቤቶች ሲፈተሹና ሲበረበሩ ያድራሉ፤ ለዚሁ ስራ ለአንድ ወር ሲሰለጥኑ የነበሩ ልዩ ሀይሎች ተሰማርተዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
“ለ40 ቀናት የመንግስት መስሪያ ቤቶች መዘጋት እንዳለባቸው ሰብስበው የነገሩን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር ናቸው” ያሉት አንድ የመንግስት ሰራተኛ፤ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ማክበር የመንግስት ብቻ አለመሆኑን ከተስማማን በኋላ ሁላችሁም ወገባችሁን አስራችሁ ፍተሻ ቀጥሉ በሚል ስም ተመዝግቦና ቁጥጥር እየተደረገ የመንግስት ሰራተኛው በቡድን ተከፍሎ ፍተሻውን ተያይዞታል ብለዋል፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዲአዚዝ መሀመድ በበኩላቸው፤ መረጃው የተሳሳተ መሆኑን ገልፀው “እንዴት የመንግስት መስሪያ ቤት 40 ቀን ሙሉ ይዘጋል” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
የብሔር ብሔረሰቦችን በዓል አከባበር በተመለከተ፣ የመንግስት ሠራተኞች በትርፍ ሰዓታቸው ለሕዝቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት አገልግሎት ይሰጣሉ ካሉ በኋላ፤ “ፍተሻ አለ፣ ባጃጅ አይሰራም፣ ሰዓት እላፊ ታውጇል የሚባለው ከእውነት የራቀ ነው” ሲሉ አስተባብለዋል፡፡
 
 Written by  ናፍቆት ዮሴፍ

No comments:

Post a Comment