Thursday, November 7, 2013

ስየ አብርሃ የኢትዮዽያ ሰራዊት አሰባስቦ የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ለመገልበጥ እያሴረ ነው በሚል ህወሓቶች ተሸብረዋል ህወሓቶች ባስቸኳይ ስብሰባዎች ተወጥረዋል። ሰሞኑ በመቐለ ከተማ የደህንነቶች፣ የታማኝ ካድሬዎችና የምክርቤት ስብሰባዎች ነበሩ/አሉ። የተጨናነቁበት አንድ ጉዳይ አለ።

ህወሓቶች ባስቸኳይ ስብሰባዎች ተወጥረዋል። ሰሞኑ በመቐለ ከተማ የደህንነቶች፣ የታማኝ ካድሬዎችና የምክርቤት ስብሰባዎች ነበሩ/አሉ። የተጨናነቁበት አንድ ጉዳይ አለ። 
ህወሓቶች ካድሬዎችን ሰብሰበው የሆነ ግለሰብ ወይ አካል ዒላማ አድርገው ስሙ በማጥፋት ከህዝብ ለመነጠል ጥረት ያደርጋሉ። ቀደም ሲል “አብርሃ ደስታ የሚፅፋቸው ነገሮች ዉሸት ናቸው እያልን ህዝብ እንዳይሰማው እናድርግ” በሚል አብርሃ ደስታ በመላው ትግራይ በራሳቸው አንደበት አስተዋውቀውታል። 
አሁን ደግሞ በመላው ትግራይ ስለ ስየ አብርሃ መጥፎ በመናገር ስሙ ለማጥፋት ታቅዷል። በህወሓት መንደር ዋነኛ ስጋት የፈጠረው (ባሁኑ ሰዓት) አብርሃ ደስታ ወይ ዓረና ፓርቲ አይደለም፤ ስየ አብርሃ እንጂ። ስየ እንዴት ለህወሓቶች ስጋት ፈጠረ? ‘ስየ ከፖለቲካ ራሱ አግሏል’ እየተባለ አልነበረም? 
ከህወሓቶች የደረሰኝ መረጃ እንደሚያሳየው ስየ አብርሃ የኢትዮዽያ ሰራዊት (ከኢትዮዽያ ዉጭ በሰላም ማስከበር ተልእኮና በሌላ ምክንያት የሚገኝ) አሰባስቦ የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ለመገልበጥ እያሴረ ነው በሚል ስጋት ህወሓቶች የሚያደርጉትን ጠፍቷቸዋል። 
የአልሸባብና የኤርትራ አሸባሪ መጣ ፣፣ ምናምን እያሉ የተሸበሩም ከስየ ስጋት የተቆራኘ ነው። ስለ እውነታዊነቱ እርግጠኛ አይደለሁም። ህወሓቶች በስየ አብርሃ መሸበራቸው ግን እርግጠኛ ነው። ካሁን በኋላ ስየ በትግራይ ህዝብ ድጋፍ እንዳይኖረው ለማድረግ ህወሓቶች ስም የማጥፋት ዘመቻ ይከፍታሉ።

No comments:

Post a Comment