Friday, March 28, 2014

በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ደማቅ የተቃውሞ ትእይንት ተደረገ::

March 28, 2014
ሳዲቅ አህመድ
በአዲስ አበባ ታላቁ አንዋር መስኪድን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪቱ ዋናዋና ከተሞች ‹‹ሰላታችንን በመስጂዳችን!›› በሚል መሪ ቃል ህዝበ ሙስሊሙ እያካሄደው ያለው መስጂድ ተኮር የዘመቻ እንቅስቃሴ አካል የሆነው እና የዘመቻው ማጠናቀቂያ የጁምኣ የተቃውሞ ትእይንት በደመቀ መልኩ ተካሂዷል::Ethiopian Muslims protest, Addis Ababa (March 28, 2014)
ህዝቡን ከመስጂዱ ለመነጠል በመንግስት በኩል እየተሰራ ያለውን ህገ ወጥና ኢ-ህገ መንግስታዊ ስራም ለራሱ ተረድቶ ላልሰሙት ሁሉ በማሰማትና መስጂዶቹን በዒባዳ በማድመቅ ላይ ነው የሚገኘው፡፡ ይህ ወቅታዊና አንገብጋቢ የመስጂድ ባለቤትነትን የማረጋገጥ እንቅስቃሴ የመንግስትን እና የመጅሊስን ሴረኞች እንቅልፍ ማሳጣቱንም ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡ የውስጥ መረጃዎች እያጋለጡ ነው፡፡ ‹‹ሰላታችንን በመስጂዳችን!››ዘመቻ የዛሬው ጁሙአ ድረስ ቀጥሎ የቆየ ሲሆን በአዲስ አበባና በተመረጡ የክልል መስጂዶች ላይም አስቀድሞ የነበሩንን ቋሚ ትዝታ ጥለው ያለፉ ግዙፍ ተቃውሞዎችን በሚያስታውስ መልኩ የደመቀ የተቃውሞ ስነስርአት በማድረግ በሰላማዊ ሁኔታ ዘመቻው መጠናቀቁ ታውቋል::
በዚህም መሰረት ከቀኑ ስድሰት ጀምሮ በአዲስ ወደ አዲስ አበባ አንዋር መስኪድ እና በተለያዩ ከተሞች በሚገኙ የተቃውሞ ወደተመረጡ መስኪዶች የተመመው ህዝበ ሙስሊሙ የመስኪዶችን ውስጥ እና ደጅ በመሙላት መስኪዶቹ የራሱ ሃብት መሆናቸውን እና ሙስሊሙ ህዝብ ሰላም ፈላጊ መሆኑን በደመቀ ተቃውሞ ነጭ ምልክቶችን በማውለብለብ ገልጿል::
ህዝበ ሙስሊሙ ዘመቻውን በተሳካ መልኩ በማድረግ ሰላማዊ ተቃውሞውን አሰምቶ ከኮሚቴው ጎን ዛሬም ቃሉን አክብሮ እንደቆመ በማሳየት በሰላም መመለሱን ለማረጋገጥ ተችሏል:: [ተጨማሪ ፎቶዎችን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ] [ቪዲዮዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
]http://ecadforum.com/Amharic/archives/11586/


Wednesday, March 26, 2014

Ethiopia: Arrests and Detentions of Oromo Students in Southern Oromia

Wednesday, March 26, 2014


Ethiopia: Arrests and Detentions of Oromo Students in Southern Oromia

hrlha

HRLHA Urgent Action
March 26, 2014
Human Rights League of the Horn of Africa (HRLHA) would like to express its deep concern over the safety and fates of Shakiso High School Oromo Students who became victims of discriminate mass arrest and detention in Shakiso Town of Guji Zone in southern Oromia. Around two hundred ethnic Oromo Students have been sent to a jail in the nearby Adola Town, and some have received varying degrees of injuries both from bullets that were shot by the security forces during the interference and by beatings.
Shakiso High School

Shakiso High School
Those high school Oromo Students, almost all of whom are juvenile, were arrested and/or picked up at different times from different places including the school compound following a minor clash between them and ethnic Amhara Students of the same high school. According to information obtained by HRLHA through its correspondents, the clash between the two groups occurred following a provocation by the ethnic Amhara Students in opposition to the singing of the regional anthem in the regional Oromo Language by ethnic Oromo Students during flag raising ceremony at the school based on the rules and regulations provided for by the constitution of the regional state. The ethnic Oromo Students were reporting the incident and filing their complaints with the school administration when the school compound was raided by the federal security forces. Among the ironies surrounding this incident were that:
  1. The Federal Security Forces were deployed to interfere in such very minor and localized issues that could easily be dealt with by local administrative bodies and communities including that of the school itself,
  2. The ethnic Oromo Students, who were the victims of the clash, were discriminately double-victimized while those who triggered the violence were left unquestioned,
  3. Not only that such constitutional provisions as a regional anthem that have been in place for close to two decades becomes a subject of dispute, but also those who attempted to exercise such legal provisions were deemed criminals that belong to detention instead of those who contradicted the constitution head on.
The Human Rights League of the Horn of Africa (HRLHA) has been able to obtain the names of the
following Oromo students among those who have been detained:
  1. Bezabish Gurmeessaa (MEMBER OF OPPOSITION OFC)- wounded by bullet,
  2. Desta Waaree – beaten up and injured,
  3. Bali Chachu (MEMBER OF OPPOSITION OFC)
  4. Buno Shaggola (MEMBER OF OPPOSITION OFC)
  5. Bakalcha Oddo (MEMBER OF OPPOSITION OFC)
  6. Bezabish Gurmeessaa
  7. Chaltu Birbissa
  8. Hotessa Soree
  9. Yohanes Jisso
  10. Kifle Areri
  11. Badhadha (father name not identified)
  12. Beyena Jarso
  13. Shambel Galchu
  14. Jemal Aga
  15. Wendimu Areri
  16. Nagessa Gedo
  17. Getachew Demise
  18. Boru Dube
  19. Gemechis Bilu
  20. Chari Chana
  21. Ware Kottola ,
Although the interference of the government security forces was not far from expectations, the very harsh and violent actions that have resulted in life-threatening injuries are not acceptable by any standard. Given the violent way the students were dealt with, it is also very likely that they could be subjected to tortures.

Therefore, HRLHA calls up on the Ethiopian government to unconditionally release the detained
students; and allow necessary treatments for those who have been injured and/or wounded. It also calls upon the Ethiopian government to investigate the clash and bring the culprits to justice so that they refrain from continued racist provocations that will create conflicts between the two nations.
http://ayyaantuu.com/horn-of-africa-news/oromia/ethiopia-arrests-and-detentions-of-oromo-students-in-southern-oromia/   

Tuesday, March 25, 2014

የኢትዮጵያ መንግስት በውጭና በአገር ውስጥ የሚገኙ ፖለቲከኞችንና ጋዜጠኞችን ይሰልላል ተባለ

March 25, 2014
መጋቢት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሂውማን ራይትስ ወች ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በአገር ውስጥ እና በውጭ የሚኖሩ ፖለቲከኞችንና ጋዜጠኞችን ይሰልላል ብሎአል።

ድርጅቱ ባወጣው ባለ 100 ገጽ ሪፖርት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለስርአቱ አደገኛ ናቸው ብሎ የሚያስባቸውን በውጭና በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎችን ለመሰለል ከተለያዩ አገሮች ቴክኖሎጂዎችን ማስገባቱን ” ገልጿል።

የመንግስት ድርጊት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ በነጻነት የመደረጃትና መረጃ የማግኘት መብትን እንደሚጥስ የገለጸው ሂውማን ራይትስ ወች፣ መንግስት ሙሉ በሙሉ በሚቆጣጠረው ቴሌኮሚኒኬሽን አማካኝነት የስለላ ስራውን እንደሚሰራ አመልክቷል።

ለኢትዮጵያ መንግስት የቴክኖሎጂ ውጤቶችን የሚሸጡ ድርጅቶች ፣ መንግስት በህገ ወጥ መንገድ ለሚያደርገው ስለላ ድጋፍ እየሰጡ ነው” በማለት የድርጅቱ የቢዝነስና የሰብአዊ መብቶች ዳይሬክተር የሆኑት አርቪድ ጋንሲያን ተናግረዋል።

ሪፖርቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች እንዲሁም የቀድሞ የደህንነት ሰራተኞችን በማነጋገር የተጠናቀረ ነው፤፡መንግስት በወንጀል የጠረጠራቸውን ሰዎች አስሮ በሚያሰቃይበት ጊዜ ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ የጠለፋቸውን ስልኮች በማስረጃነት አቅርቦ እንደሚያሰማ እንዲሁም ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፎች በሚደረጉበት ጊዜ የስልክ መስመር ( ኔት ወርክ) እንደሚጠፋ ድርጀቱ በሪፖርቱ አመልክቷል።

ለስለላ ተግባር የሚውሉት አብዛኞቹ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ከቻይናው ዜቲኢ መገኘቱን ሪፖርት፣አመልክቷል፡፡ እንዲሁም ተቀማጭነቱን በዩናይትድ ኪንግደምና በጀርመን ካደረገው ጋማ ኢንተርናሽናል ፊን ፊሸርን፣ ከጣሊያኑ ሃኪንግ ቲም ከርቀት ለመቆጣጠር የሚያስችል መሳሪያ አግኝታለች።

Ethiopia: Telecom Surveillance Chills Rights A new report from Human Rights Watch says Ethiopia is using some of the world's most advanced surveillance software to monitor communications from Ethiopians at home and abroad.

Foreign Technology Used to Spy on Opposition inside Country, Abroad
MARCH 25, 2014
The Ethiopian government is using control of its telecom system as a tool to silence dissenting voices. The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses.
Arvind Ganesan, business and human rights director
(Berlin) – The Ethiopian government is using foreign technology to bolster its widespread telecom surveillance of opposition activists and journalists both in Ethiopia and abroad.

The 100-page report“‘They Know Everything We Do’: Telecom and Internet Surveillance in Ethiopia,” details the technologies the Ethiopian government has acquired from several countries and uses to facilitate surveillance of perceived political opponents inside the country and among the diaspora. The government’s surveillance practices violate the rights to freedom of expression, association, and access to information. The government’s monopoly over all mobile and Internet services through its sole, state-owned telecom operator, Ethio Telecom, facilitates abuse of surveillance powers.

“The Ethiopian government is using control of its telecom system as a tool to silence dissenting voices,” said Arvind Ganesan, business and human rights director at Human Rights Watch. “The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses.”

The report draws on more than 100 interviews with victims of abuses and former intelligence officials in Ethiopia and 10 other countries between September 2012 and February 2014. Because of the government’s complete control over the telecom system, Ethiopian security officials have virtually unlimited access to the call records of all telephone users in Ethiopia. They regularly and easily record phone calls without any legal process or oversight.

Recorded phone calls with family members and friends – particularly those with foreign phone numbers – are often played during abusive interrogations in which people who have been arbitrarily detained are accused of belonging to banned organizations. Mobile networks have been shut down during peaceful protests and protesters’ locations have been identified using information from their mobile phones.

A former opposition party member told Human Rights Watch: “One day they arrested me and they showed me everything. They showed me a list of all my phone calls and they played a conversation I had with my brother. They arrested me because we talked about politics on the phone. It was the first phone I ever owned, and I thought I could finally talk freely.”

The government has curtailed access to information by blocking websites that offer any independent or critical analysis of political events in Ethiopia. In-country testing that Human Rights Watch and Citizen Lab, a University of Toronto research center focusing on internet security and rights, carried out in 2013 showed that Ethiopia continues to block websites of opposition groups, media sites, and bloggers. In a country where there is little in the way of an independent media, access to such information is critical.

Ethiopian authorities using mobile surveillance have frequently targeted the ethnic Oromo population. Taped phone calls have been used to compel people in custody to confess to being part of banned groups, such as the Oromo Liberation Front, which seeks greater autonomy for the Oromo people, or to provide information about members of these groups. Intercepted emails and phone calls have been submitted as evidence in trials under the country’s flawed anti-terrorism law, without indication that judicial warrants were obtained.

The authorities have also detained and interrogated people who received calls from phone numbers outside of Ethiopia that may not be in Ethio Telecom databases. As a result, many Ethiopians, particularly in rural areas, are afraid to call or receive phone calls from abroad, a particular problem for a country that has many nationals working in foreign countries.

Most of the technologies used to monitor telecom activity in Ethiopia have been provided by the Chinese telecom giant ZTE, which has been in the country since at least 2000 and was its exclusive supplier of telecom equipment from 2006 to 2009. ZTE is a major player in the African and global telecom industry, and continues to have a key role in the development of Ethiopia’s fledgling telecom network. ZTE has not responded to Human Rights Watch inquiries about whether it is taking steps to address and prevent human rights abuses linked to unlawful mobile surveillance in Ethiopia.

Several European companies have also provided advanced surveillance technology to Ethiopia, which have been used to target members of the diaspora. Ethiopia appears to have acquired and used United Kingdom and Germany-based Gamma International’s FinFisher and Italy-based Hacking Team’s Remote Control System. These tools give security and intelligence agencies access to files, information, and activity on the infected target’s computer. They can log keystrokes and passwords and turn on a device’s webcam and microphone, effectively turning a computer into a listening device. Ethiopians living in the UK, United States, Norway, and Switzerland are among those known to have been infected with this software, and cases have been brought in the US and UK alleging illegal wiretapping. One Skype conversation gleaned from the computers of infected Ethiopians has appeared on pro-government websites.

Gamma has not responded to Human Rights Watch inquiries as to whether it has any meaningful process in place to restrict the use or sale of these products to governments with poor human rights records. While Hacking Team applies certain precautions to limit abuse of its products, it has not confirmed whether and how those precautions applied to sales to the Ethiopian government.

“Ethiopia’s use of foreign technologies to target opposition members abroad is a deeply troubling example of this unregulated global trade, creating serious risks of abuse,” Ganesan said. “The makers of these tools should take immediate steps to address their misuse; including investigating the use of these tools to target the Ethiopian diaspora and addressing the human rights impact of their Ethiopia operations.”

Such powerful spyware remains virtually unregulated at the global level and there are insufficient national controls or limits on their export, Human Rights Watch said. In 2013, rights groups filed acomplaint at the Organization for Economic Co-operation and Development alleging such technologies had been deployed to target activists in Bahrain, and Citizen Lab has found evidence of use of these tools in over 25 countries.

The internationally protected rights to privacy, and freedom of expression, information, and association are enshrined in the Ethiopian constitution. However, Ethiopia either lacks or ignores judicial and legislative mechanisms to protect people from unlawful government surveillance. This danger is made worse by the widespread use of torture and other ill-treatment against political detainees in Ethiopian detention centers.

The extent of Ethiopia’s use of surveillance technologies may be limited by capacity issues and a lack of trust among key government ministries, Human Rights Watch said. But as capacity increases, Ethiopians may increasingly see far more pervasive unlawful use of mobile and email surveillance.

The government’s actual control is exacerbated by the perception among many Ethiopians that government surveillance is omnipresent, resulting in considerable self-censorship, with Ethiopians refraining from openly communicating on a variety of topics across telecom networks. Self-censorship is especially common in rural Ethiopia, where mobile phone coverage and access to the Internet is very limited. The main mode of government control is through extensive networks of informants and a grassroots system of surveillance. This rural legacy means that many rural Ethiopians view mobile phones and other telecommunications technologies as just another tool to monitor them, Human Rights Watch found.

“As Ethiopia’s telecom system grows, there is an increasing need to ensure that proper legal protections are followed and that security officials don’t have unfettered access to people’s private communications,” Ganesan said. “Adoption of Internet and mobile technologies should support democracy, facilitating the spread of ideas and opinions and access to information, rather than being used to stifle people’s rights.”

http://www.hrw.org/

Monday, March 24, 2014

(ይህ “ኑ! እንዋቀስ” የሚለው ስር ነቀል የለውጥ ጥሪ ቀጥታ የሚያነጣጥረው በኢህአዴግ አባላት ላይ ብቻ ነው፤ አመራሩን በፍፁም አይመለከትም) ኢህአዴግ ራሱ በይፋ ሲናገር እንደተደመጠው፣ በአሁኑ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ገደማ ደርሷል፡፡ ይህም የአገሪቱ ቁጥር አንድ ግዙፍ የፖለቲካ ፓርቲ ያደርገዋል፡፡ በርግጥ ግዙፍ እንጂ ጠንካራ እንዳላልኩ ልብ ይሏል፡፡ ምክንያቱም ጥንካሬ የሚለካው በአባላት ቁጥር ሳይሆን በድርጅት ፍቅር፣ በዓላማ ፅናትና በሚሰጡት ልባዊ አበርክቶ ነው፡፡ እንዲህ ያለ አቋመ-ብርቱነት ደግሞ ድሮ በያ ትውልድ

394711_184013551696255_1365830121_n(ይህ “ኑ! እንዋቀስ” የሚለው ስር ነቀል የለውጥ ጥሪ ቀጥታ የሚያነጣጥረው በኢህአዴግ አባላት ላይ
ብቻ ነው፤ አመራሩን በፍፁም አይመለከትም)
ኢህአዴግ ራሱ በይፋ ሲናገር እንደተደመጠው፣ በአሁኑ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ገደማ
ደርሷል፡፡ ይህም የአገሪቱ ቁጥር አንድ ግዙፍ የፖለቲካ ፓርቲ ያደርገዋል፡፡ በርግጥ ግዙፍ እንጂ ጠንካራ
እንዳላልኩ ልብ ይሏል፡፡ ምክንያቱም ጥንካሬ የሚለካው በአባላት ቁጥር ሳይሆን በድርጅት ፍቅር፣
በዓላማ ፅናትና በሚሰጡት ልባዊ አበርክቶ ነው፡፡ እንዲህ ያለ አቋመ-ብርቱነት ደግሞ ድሮ በያ ትውልድ
ጊዜ ቀርቷል፡፡ በዘመነ-ኢህአዴግ የተንሰራፋው ጥቅመኝነት (በእነርሱ ቋንቋ ኪራይ ሰብሳቢነት) ብቻ
ነው፡፡ ለዚህም በደቡባዊቷ አዋሳ ከተማ ስድስተኛው የድርጅቱ ጉባኤ በተካሄደበት ወቅት፣ አቶ በረከት
ስምኦን በብስጭት እየተትከነከነ በደፈናው ለጥቅም ድርጅቱን የተቀላቀሉ አባላት በርካታ መሆናቸውን
አምኖ በአደባባይ መናገሩ አስረጂ ሊሆነን ይችላል፡፡ ይህን ንግግሩንም አፍታተን ስናብራራው
እንደሚከተለው ሆኖ እናገኘዋለን፡- የግንባሩ አባላት ቁጥር ሰባት ሚሊዮን ገደማ የደረሰው በጥቅም በመደለል፣ በአንድ ለአምስት የጥርነፋ
መዋቅር በፍርሃት ተጠፍንጎ በመያዙና በመሳሰሉት ነው (መቼስ አቶ በረከት ከድርጅቱ ጉምቱ መሪዎቹ አንዱ ነውና ዘርዝሮ እንዲያስረዳን
አይጠበቅበትም)
የሆነው ሆኖ አባላቱ እንዲህ የመብዛታቸው ምስጢር የድርጅቱ አምባ-ገነንነት ባህሪይ መገለጫ እንጂ አመላይ አጀንዳ አሊያም
ምትሀታዊ ችሎታ እንዳለው የሚያሳይ አይደለም፡፡ ይህ የትኛውም መሰል ሥርዓት ከተጠናወተው ሁሉንም ከመቆጣጠርና መጠቅለል
(Totalitarianism) አስተሳሰብ የሚሰርፅ ማኪያቬሊያዊ አስተምህሮ ነው፡፡ የሆነው ሆኖ ‹‹አምባገነኖች የአንድ እናት መንትያ ልጆች
ናቸው›› እንዲሉ፤ በ‹‹ቆራጡ መሪ›› ዘመነ-መንግስትም በጊዜው ከነበረው የሀገሪቱ ሕዝብ ቁጥር አኳያ መሳ-ለመሳ ሊባል በሚያስደፍር
ሁኔታ ሳር ቅጠሉ ሁሉ ሰማያዊ ካኪ ለባሽ የኢሠፓ አባል ሆኖ ነበር፡፡ ግና፣ ያ ካኪ ለባሽ ሕዝብ፣ የልቡን በልቡ ይዞ ‹‹ቪቫ መንጌ!›› እያለ
አሳስቆ በስተመጨረሻ ጉድ እንደሰራው ሁሉ፤ ‹‹ይህ የህዝብ ማዕበል…›› ተብሎ በአቶ መለስ ዜናዊ የተሞካሸው የ97ቱ የቅዳሜው መሬት
አንቀጥቅጥ የሰልፍ ትዕይንትም፣ በድጋፍ ሳይሆን በግዳጅ የሰመረ መሆኑን ለማየት፤ አይቶም ለመመስከር ከሃያ አራት ሰአት ጊዜ በላይ
አልወሰደብንም፡፡ እንዴት? ቢሉ በማግስቱ (ሚያዚያ 30) ለተቃውሞ ከወጣው ሕዝብ የቅዳሜዎቹም በብዛት መሳተፋቸውን በራሳቸው
አንደበት ‹‹ትላንት ለቲሸርት፤ ዛሬ ለነፃነት!›› በሚል ሕብረ-ዝማሬ ከአደባባዩም አልፎ ከተማዋን በሚያናውፅ የለውጥ ጩኸት
የመሰከሩበት ‹‹ፖለቲካ›› መቼም ቢሆን አይዘነጋምና፡፡
እንግዲህ ይህ ሁሉ ታሪካዊ ሀቅ የሚገልፅልን አንድ ታላቅ እውነት-በጥቅም እየደለሉ አባልን ማብዛት በክፉ ቀን የማይታደግ መሆኑን ነው፡
፡ ጥቅመኝነት ግፋ ቢል የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ‹‹ፀበል›› ያስጠምቅ፣ ‹ኢህአዴግ ጌታ ነው!›ን ያስፎክር ያሸልል ይሆናል እንጂ
የኢትዮጵያን ትንሳኤ መሻትን አያስቀይርም፡፡ ነብር ዥንጉርጉርነቱን እንደማይለውጠው ሁሉ የኢህአዴግ አባላትም ምንም ቢሆን ምን፣
እንደሌላው ሕዝብ የሀገር አንድነት የሚያሳስባቸው፣ ብሔራዊ ውርደት (ረሀብተኝነት) በቁጭት የሚያንገበግባቸው፣ ከዘውግ ልዩነት
የሕዝብ ለሕዝብ መተማመንና አንድነታዊ ጥንካሬው የሚበልጥባቸው፣ የኃይማኖት ነፃነት የሚያስተቃቅፋቸው… ናቸው ብዬ አምናለሁ፡፡
ምክንያቱም ጥቅመኝነት የእጦትን ክፍተት ለመሙላት ለጊዜው ያሰግዳል እንጂ ክብርንና ማንነትን አስሽጦ በባርነት ቀንበር አያሳድርም-
በተለይም ዥንጉርጉርነቱን ጠንቅቆ ለሚያውቀው ኩሩ-ሀበሻ!
ደግሞስ ምን ያህሉ አባል ነው፣ የድርጅቱን መታወቂያ በመያዙ ብቻ የረባ ጥቅም ያገኘው? በግላጭ እንደሚታየው በግል ጥቅምም ሆነ
በተጭበረበረው የዘውግ ፖለቲካ ሳቢያ ኢህአዴግን የተቀላቀሉ የአብዛኞቹ አባላት የኑሮ ደረጃ ዛሬም እንደ ብዙሃኑ የኢትዮጵያ ህዝብ
ከችግር የመቆራመድ አስከፊ ሕይወት አልተላቀቀም፡፡ ፓርቲውን መታከካቸውም በማይጨበጥና በማይታይ እንቅልፍ የለሽ ሕልም
አናውዞ ይበልጥ ደቁሷቸዋል እንጂ በቀን ሶስቴ መመገብ እንኳ አላስቻላቸውም፡፡ ሌላው ቀርቶ የድርጅት አባልነታቸው እንደተርታው
ሕዝብ በአድሎአዊ አሰራር መማረርን እንዳላስቀረላቸው በርግጠኝነት መመስከር ይቻላል፡፡
ይህ አይነቱም እርግጠኝነት ነው ‹ኑ! እንወቃቀስ (እንነጋገር)፤ እንተማመንምና ሀገርና ትውልድ እየገደለ ያለውን ፓርቲያችሁን አብረን
ተጋግዘን እናፍርሰው› የሚል የማንቂያ ደውል ላሰማችሁ ገፊ-ምክንያት የሆነኝ፡፡ እናም ድርጅታችሁን ትመረምሩ ዘንድ ወደድኩ፡-
ድርጅታችሁ ሥልጣን ላይ ተፈናጥጦ ባሳለፋቸው ሁለት አስርታት የተጓዘበትን መንገድ በአስተውሎት ብትመረምሩ፤ በእርግጠኝነት እንደ
ግዙፍ ዐለት ካገጠጡ ሀገራዊ ውድመቶች እና ከበባድ ኪሳራዎች ጋር መፋጠጣችሁ አይቀሬ ነው፡፡ ይህም ሆኖ በቅድሚያ በተልካሻ
ፕሮፓጋንዳ ያሰለቸንን የብሔር ጉዳይ (የተወሰኑ ሰዎችን አማልሎ አባል ለማድረግ አስተዋፆ እንዳለው ባይካድም) ወደጎን ብለን፤
የትኛውም ብሔረሰብ ባህላዊ እሴቶቹን ማክበር፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋው መጠቀም… የፖለቲካ ፓርቲ በችሮታ የሚሰጠው ሳይሆን፣
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
2
የማንም ተፈጥሮአዊ መብት መሆኑን ማስረገጥ አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡ ይህ ማለት ግን የድርጅታችሁ ሀቲት፡- ‹አንዱ በሌላው እድሜውን
ሙሉ ሲጨቆን እንደኖረ፤ ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተለየ እንደሆነ፤ ከብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማችን ይልቅ የክልሉን እንዲያስቀድም
መቀስቀስና መስበክን የብሔር ብሔረሰብ መብትን ማክበር ነው› የሚለውን አምኖ መቀበል አይደለም፡፡ በግልባጩ ስርዓቱ እንዲህ አይነት
ጉዳዮችን ሰማይ ጥግ አጉኖ፣ ሕዝብን ከፋፍሎና በጥርጣሬ (በጎሪጥ) ወደሚተያይበት ጠርዝ ገፍቶ፣ የሥልጣን ዕድሜውን ያራዘመበት
ሁለት አስርታትን ያሳለፈ ስልቱ መሆኑን መረዳት አይሳናችሁም ብዬ አስባለሁ፡፡
ሌላ ሌላውን ትተን እንኳ የኢህአዴግን አመሰራረት ብንመለከት ግንባሩን ከፈጠሩት አራቱ ድርጅቶች መካከል ከሞላ ጎደል ህወሓት እና
ኢህዴን/ብአዴንን እንደ ፖለቲካ ድርጅት መውሰድ ይቻል ይሆናል እንጂ፤ ኦህዴድና ደኢህዴን፣ በህወሓት ‹‹አባ መላ››ዎች እንደ
የፋብሪካ ሳሙና በሚፈለጉበት መጠንና ቅርፅ ተጠፍጥፈው ከተሰሩ በኋላ በኦሮሞና በደቡብ ኢትዮጵያ ተወላጆች ላይ እንደ አለቅት
የተጣበቁ የመሆናቸውን ምስጢር እነርሱም ራሳቸው የሚክዱት አይመስለኝም (ምናልባት በሽግግሩ የመጀመሪያ ዓመት ላይ
እንደአስተዋልነው ከኦህዴድ ይልቅ፣ ኦነግ ኦሮሚኛ ተናጋሪዎችን ወክሎ ቢቀጥል ኖሮ ይህ ጉዳይ በዚህ አውድ ላይነሳ ይችል ነበር፡፡ የሆነው
ግን ተቃራኒው ነው፤ የራሱ የፖለቲካ ቁመናና ራዕይ የነበረው በኃይል ተገፍቶ፤ በምትኩ በሌሎች እስትንፋስ ህልው ሆኖ
‹‹የሚያስተዳድረው››ን ሕዝብና ራሱንም ጭምር ቀን ከሌት ‹‹ከብሔር ጭቆና ነፃ አወጣናችሁ›› ስለሚሉት ሞግዚቶቹ ገድል መተረክን
‹‹ፖለቲከኛነት›› አድርጎ የወሰደው ኦህዴድን ያነገሰ ነውና)
በነገራችን ላይ የፖለቲካ ፓርቲን እንደ ፋብሪካ ምርት ጣጣ-ፈንጣጣው ተጠናቅቆለት ሲያበቃ የመጫኑ አሰራር በሁለቱ ክልሎች ብቻ
ተገድቦ የቀረ አይደለም፤ አጋር ፓርቲዎችንም ይመለከታል፡፡ ከአፋር እስከ ጋምቤላ እና ቤንሻንጉል፤ ከሀረር እስከ ሶማሌ ሲተገበር
በትዝብት የተመለከትነው ጉዳይ ነው፡፡ መቼም ገና ከስር መሰረቱ ‹‹እኛ እናውቅልሀለን!›› በሚሉ ‹‹የፖለቲካ ሞግዚቶች›› የተፈጠረ
ድርጅት በምደባ ቦታውን ያገኙ የአመራር አባላቱን በቅምጥል ኑሮ ከማንፈላሰስ በዘለለ፣ ‹‹እወክለዋለሁ›› ለሚለው ሕብረተሰብ ትርጉም
ያለው ስራ ይሰራል ተብሎ የሚታሰብ አይደለምና ‹በኦሮሚያ ሙስና እንደሰላምታ እጅ መጨባበጥ ተዘውታሪና ተራ ነገር ነው›፣ ‹በአፋር
ባጀት መቀለጃ ሆኗል›፣ ‹በሐረር ቤተሰባዊ ኢምፓየር ተገንብቷል›፣ ‹ቤንሻንጉል በድህነት ማቀቀ›፣ ‹ሶማሌ ክልል የአስተዳዳሪው አብዲ
ርስተ-ጉልት ሆነ› ጂኒ ቁልቋል እያሉ ሮሮዎችን ማሰማት ለውጥ አያመጣም፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ህወሓትን እንደ ‹‹ግል አዳኝ››
በመቀበላቸው ብቻ ‹‹የአስተዳዳሪነት›› ካባ የተደረበላቸው ምስኪን የአመራር አባላት በቀላል ጉዳይ ላይ እንኳ የመወሰን ሥልጣን
የላቸውምና ነው፡፡
ይህ እንግዲህ በቀጥታ ከኢህአዴግ ስነ-ተፈጥሮ ጋር የሚጋመድ ችግር ነው፡፡ ሆኖም የመንግስት ሥልጣን መዘውር ከጨበጠ በኋላ
የጨፈለቃቸውን የዴሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶች ተከትሎ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የደረሱ የአያሌ ሰላማዊ ዜጐች ግድያ፣ እመቃ፣
ከስራና ቤት ንብረት መፈናቀል፣ ስደትን… አንድ በአንድ ጠቅሰን ለማውገዝ ብንሞክር ሰማይ-ብራና፣ ቀይ ባህር-ቀለም ሆነው
ካልተመቻቹልን በቀር የሚደፈር አይመስለኝም፡፡ በርግጥ በኢህአዴግ ውስጥ ታላቅና ታናሽ ንጉሠ-ነገሥት የሆኑት ህወሓትና ብአዴን
ብረት ነክሰው፣ ሳንጃ ወድረው በትጥቅ ትግል ያለፉ ከመሆናቸው አኳያ ለየትኛውም አይነት ቅራኔም ሆነ ልዩነት ከመግደልና መጋደል
ውጪ ያለ ሌላ ሰላማዊ አማራጭ ላይዋጥላቸው እንደሚችል መዘንጋት የለበትም፡፡ ኦነግ ከሽግግር መንግስቱ ከተገፋበት ጊዜ አንስቶ
በኦሮሚያ፣ በአዋሳ፣ በሶማሌ… ግፉአን ያለቁበትን፤ እንዲሁም በድህረ-ምርጫ 97 የታየው የጎዳና ላይ ጭፍጨፋ ይህንኑ ሀቅ ያስረግጣሉ፡፡
ኩነቱም ግንባሩ በመጣበት አይነት የነፍጥ የበላይነት ያለፉት ሶቪየት ህብረት፣ ቻይና፣ ቬትናም፣ ኩባ፣ ኤርትራ ባሉ ሀገራት ከታየው
የሕዝቦች እልቂት፣ የተቀናቃኝ ድምፆች መታፈን፣ የጋዜጠኞች መጨፍለቅ… ጋር ቀጥታ ዝምድና አለው፡፡ እነዚህ ሀገራትንም ሆነ
ኢህአዴግን የተለየ ሃሳብ ለማስተናገድ ትዕግስቱም ፍላጎቱም እንዳይኖራቸው ያደረገው ይህ ከውልደታቸው ጀምሮ ከደም-አጥንታቸው
ጋር የተዋሃደው ተፈጥሮአቸው ይመስለኛል፡፡
በአናቱም ኢህአዴግ ከአባላቱ ይልቅ የአመራሩ ‹‹ፓርቲ›› ብቻ ስለመሆኑ ለመረዳት የውስጥ አሰራሩን መፈትሽ የተሻለ ይሆናል፤
እናንተም በቅርበት እንደምታውቁት በድርጅቱ ያልተፃፈ ሕግ ከላይ ወደታች የሚወርድ መመሪያን ትክክል ሆነም አልሆነ ‹‹ለምን?›› ብሎ
መጠየቅ የሚያስቀስፍ ሀጢያት ነው፡፡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመወያየት መሻት፣ ጥያቄ ማቅረብ፣ ሃሳብን መቃወም፣ ስህተቶችን
ማጋለጥ… አሳድዶ በድንጋይ የሚያስወግር አሊያም ከሀገር ሀገር የሚያሰድድ ታላቅ ጥፋት ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ ይህ ሁናቴም ነው
የአስተዳደር ድክመቶቹንም ሆነ አውዳሚ ጉድለቶቹን በፍጹም ለሕዝብ እንዳይደርሱ ገትሮ መያዝን የማይዘናጋበት ዋነኛ መንግስታዊ ስራ
ያደረገው (የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞችን እና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በውሃ ቀጠነ ወደ እስር ቤት ሲያግዝ መክረሙን ልብ ይሏል)
በጥቅሉ ድርጅቱ ለአመራሮቹ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በተደረገባቸው ዘመናዊ “V8” መኪናዎች እንዲምነሸነሹ እና በቢሊዮን
የሚቆጠር የሀገር ሀብት እንዲዘርፉ የሚያስችል ስልጣን ከማጎናፀፉ ባለፈ፤ እናንተ (ብዙሀኑ አባላት) ያተረፋችሁት ምንድር ነው?
በአነስተኛና ጥቃቅን ከመደራጀት፣ ‹‹ኮብል-ስቶን›› ፈልጦ ከመደርደር የዘለለስ ማን ምን ሊጠቅስ ይችላል? እስቲ! የተራቆተችና በድህነት
ወጀብ የተንገላታች ሀገራችሁን በዓይነ-ልቦናችሁ ለማስተዋል ሞክሩ፡፡ ያን ጊዜም ገና ጀንበር ስታዘቀዝቅ ስጋቸውን ለመቸርቸር ጎዳናዎችን
የሚያጥለቀልቁ እምቦቀቅላ እህቶቻችን፣ ‹‹ማምሻም ዕድሜ ነው›› እንዲሉ የመፅዋች ዓይን እየገረፋቸው በልመና ቁራሽ ሕይወታቸውን
ለማቆየት የሚውተረተሩ አዛውንትና ህፃናት፣ በየጎዳናው በየሰፈሩ ሲንገላወዱ የሚውሉ ስራ-አጥ ወጣቶች፣ በቀን አንዴ ለመመገብ ላይ
ታች የሚማስኑ ለፍቶ አዳሪዎች… ምድሪቷን እንዳጨናነቋት ይገለፅላችኋል፡፡ የዚህ ሁሉ መንስኤም የፈጣሪ ቁጣ ሳይሆን ፅንፈኛው
3
ድርጅታችሁ በሚከተለው በተግባር ያልተፈተነ (የሀገሪቱን ተጨባጭ እውነት ያላገናዘበ) ርዕዮተ-ዓለም፣ ፖሊሲ፣ አድሎአዊ አሰራር፣
ሙስና እና ለኃላፊነት የማይመጥኑ ‹‹አስፈፃሚዎች›› ችግር ስለመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ጥርጣሬ አይግባችሁ፡፡ እናም ጉዳዩ የሀገር ነውና
በግልፅ እንወቃቀስ (እንነጋገር)፤ ስለምንድነው በአባልነት በምታገለግሉት ኢህአዴግ የሚመራው መንግስት ‹ዛሬም በስኬት ጎዳና
እየጋለብኩኝ ነው› ብሎ እንደ ቁራ እየለፈፈ በተግባር ግን፡- መብራት፣ ውሃ፣ መንገድ፣ ኔት-ወርክ እንደ አደይ አበባ በዓመት አንዴ ብቻ
ብቅ የሚለው? በአገልግሎት ተቋማት መጠቀምስ እንዲህ የአሲምባን ያህል ያራቀው ማን ነው? ፍትሕን የጠሉትን መበቀያ መሳሪያ
አድርገው ያረከሱት እነማን ናቸው? ሰርቶ መብላት የማይጨበጥ ጉም የሆነብንስ በማን የተነሳ ነው? …በርግጥ ይህንን ጥያቄ ለጠቅላይ
ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ብናቀርብለት እንደ መለስ ዜናዊ በተረት መሳለቁ ባይሆንለትም፣ ‹‹ሰለሜ ሰለሜ››ን እየጨፈረ፤
እነ‹‹ሚካኤል ስሁል›› በቀደዱለት ልክ ዳናኪራውን እያስነካው ‹‹ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም!›› ብሎ ከመዘባበት አይመለስም፡፡
መቼስ እንደዚህ ሕዝብ የተናቀ የትም አይገኝም፡፡
ኢህአዴግ መፍረስ ያለበት ለምንድን ነው?
ይህንን አጀንዳ ለማንሳት መግፍኤ የሆነው ከላይ ለማሳያ ያህል የተጠቀሱት ስርዓታዊ ጥፋቶች በግላጭ የመታየታቸው እውነታ ብቻ
አይደለም፤ ይልቁንም ድርጅቱ ከስሁት መንገዱ ለመታረም (ለመታደስ) ፍፁም ዝግ-በር የመሆኑ ጉዳይ ጭምርም ነው፡፡ አዎን፣ እነዚህ
አሁን ሁላችንንም እያማረሩ ያሉ አብዛኞቹ ችግሮች የተከሰቱት አንጋፋው ድርጅታችሁ የ‹‹ኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ
ግንባር›› የሥልጣን መሰረቱን ለማፅናት ይሁነኝ ብሎ ከደፈጠጣቸው መብቶች ጋር ተያይዘው ከመሆናቸው በዘለለ ለኢኮኖሚያዊ
ጥያቄዎች በቂ ምላሽም ሆነ ሁነኛ መፍትሔ የሌለው ፀረ-ሕዝብነቱ የተረጋገጠ፣ ለመታረም ዝግጁ ያልሆነ፣ ተስፋችንን ያሟጠጠ ስርዓት
ስለሆነም ነው፡፡ በ1970ዎቹ መጀመሪያ እነበረከት ስምኦን ልባቸው ከኢህአፓ ለመኮብለሉ አብይ ምክንያት አድርገው ያቀረቡትን ችግር
ታዬ የተባለ ታጋይ ‹‹ሞናሊዛ›› በሚለው ግጥሙ ግሩም አድርጎ ገልጦት እንደነበረ በ1993 ዓ.ም ‹‹ፅናት›› በሚል ርዕስ የተጋድሎ
ታሪካቸውን ባሳተሙበት መጽሐፍ ላይ ተርከውታል፡፡
‹‹አንተ ሌዎናርዶ የሮማ ጅል
የሰራሀትን ልታሻሽል
ልታፈርሳት ልትገነባት
ደግመህ ደጋግመህ ልትሰራት
ሰልሰህ ልትሰራት ስትችል
ጣኦት አደረግካት በሞትህ አጉል አጉል
ለራስህ ፍጡር እግዚኦ ልትል››
ይህ ግጥም በሰፈረበት ገፅ ላይ የተጠቀሰው የግርጌ ማስታወሻ ደግሞ ሊተላለፍ የተፈለገውን መልዕክት እንዲህ በማለት አብራርቶታል፡-
‹‹ታዬ የሚባል የኢህአፓ ታጋይ ‹ራሳችን የፈጠርነውን ድርጅት ማስተካከል አለብን› የሚል እምነት የነበረው ሲሆን፣ ዳ ቪንቺ እራሱ
ለሳላት ሞናሊዛ ፍቅር እንደተማረከ ሁሉ እኛም የፈጠርነውንና የተበላሸውን ድርጅት አመለክነው፤ ማስተካከልም ተሳነን በማለት ፓርቲው
ላይ እምነት ማጣቱን ‹ሞናሊዛ› በሚል ርዕስ በፃፈው ውብ ግጥም ገለፀ፡፡›› (ገፅ 61)
እነሆም አብዮታዊ ግንባሩ፣ ከመስራቾቹ አንዱ የሆነው ኢህዴን/ብአዴን፣ ያን ጊዜ ኢህአፓን መክሰሻ ባደረገበት ‹‹ድርጅታዊ አምልኮ››
ራሱም ተጠልፎ ከወደቀ ዓመታት ነጉደዋል፡፡ ታዬ እንዳለውም መሪዎቹ ኢህአዴግን ናቡከደናፆር አሰርቶት እንደነበረው አይነት እጅግ
ግዙፍ ‹‹አምላክ›› (ጣኦት) አድርገው ሀገርና ሕዝብን እየገበሩለት (እየሰዉለት) ነው፡፡ ርዕዮተ-ዓለምም ሆነ ፖሊሲ (በተለይ መሬትን
በተመለከተ) ‹‹የሚቀየረው በመቃብራችን ላይ ነው›› ሲሉም አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ የትምህርት ፖሊሲውም እንዲህ ትውልድን
እየገደለም እንዲሻሻል ያልተሞከረው በዚሁ እምነታቸው ይመስለኛል፡፡ ይህ ሁኔታም ነው እናንተም የምትስማሙባቸውን ታላላቅ ሀገራዊ
ችግሮችን ለመፍታት ኢህአዴግን ከማፍረስ ውጪ አማራጭ እንዳይኖር ያደረገው፡፡ ከእንግዲህ ወዲያም ከጥፋቱ ታርሞ ለሀገር የሚጠቅም
ዲሞክራሲያዊ የህዝብ ሥርዓት ሊያነበር ይችላል ብሎ ተስፋ ማድረግ ተላላነት ነው፡፡ እንኳን እናንተ ከተማ ላይ የተቀላቀላችሁት አባላት
ቀርቶ፣ ከበርሃ አቅፈው ደግፈው እዚህ ያደረሱት አንጋፋ ታጋዮችና አንዳንድ አመራሮቹም በድርጅቱ ተስፋ ቆርጠው ጥለውት መሄድ
ከጀመሩ ሰንብቷል፡፡ ታጋይ የውብዳር አስፋው ‹‹ፊኒክሷም ሞታ ትነሳለች›› በሚለው መጽሐፏ እውነታውን እንዲህ በማለት ገልፀዋለች፡-
‹‹የድርጅቱ አመራር የወሰዳቸውን የተሳሳቱ እርምጃዎች ቀድሞ ከነበረኝ የድርጅቱ ግንዛቤ ጋር በማጣመር ለዓመታት የታገሉለትንና
የደከሙለትን አባላት በነፃ እንዲንቀሳቀሱ ያላስቻለ ድርጅት፣ ለሕዝብ ነፃነትና ለዲሞክራሲ እታገላለሁ ቢል ከይስሙላ የማያልፍ ከንቱ
መፈክር መሆኑን ደምድሜ፣ ከመጋቢት 5 ቀን 1993 ዓ.ም ጀምሮ ራሴን ከድርጅቱ አገለልኩ፡፡ ይህም በሕይወቴ ጉዞ ዋነኛውና ወሳኝ
እርምጃ ነበር፡፡›› (ገፅ 16)
እንግዲህ ከ1968 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የድርጅት፣ የሴቶች ጉዳይና የመንግስት ሥራዎች ተሰማርታ ልጅነቷን በትግል የጨረሰችው የአቶ
ገብሩ አስራት ባለቤት፣ የውብዳር አስፋው እንዲህ አይነቱን ከባድ ውሳኔ በማሳለፍ ከኢህአዴግ ከተቆራረጠች እነሆ አስራ ሶስት ዓመታት
4
ነጉደዋል፡፡ በግልባጩ እናንተ ደግሞ እስካሁን ድረስ አንቀላፍታችኋል-ገና አልነቃችሁም፡፡ እናም እውነት እውነት እላችኋለሁ፡- ከዚህ
በላዔ-ሰብ ሥርዓት ለመገላገል የምንችለው፣ ዛሬውኑ ይህንን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ዋነኛና ወሳኝ እርምጃ በቆራጥነት መውሰድ
ስትችሉ ብቻ ነው፡፡ አለበለዚያ…
(የዚህ ጽሑፍ ሃሰበ-መልዕክትን በቅንነት ትቀበሉታላችሁ በሚል መተማመን አፈፃፀሙን፡- በምን አይነት መንገድ ተቀራርበን ልንወያይ
እንችላለን? በየትኞቹ ጉዳዮች ላይ መግባባት ይቻላል? ሃሳቡንስ ከግብ ለማድረስ ምን ያህል ጊዜ ይወስዳል? የሚሉትንና መሰል
ጥያቄዎችን በሌላ ዕትም ተገናኝተን በስፋት እንመክርባቸዋለን)
አትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ኢህአዴግ ባደባባይ የወደቀውን ፈተና “በጓሮ” አለፈ ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።

ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።
የኢህአዴግን የእውቅና ይግባኝ ጥያቄ ተቀብሎ ያጸደቀው የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የሚባለው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ነው። ተቋሙ ኢህአዴግ በ2009 አቅርቦት የነበረውን የእውቅና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ የሰጠው ምክንያት “የመያዶች ህግ የተሰኘው” አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና በአገሪቱ የተተከሉት አፋኝ ህጎች እስካልተወገዱ ድረስ ማመልከቻው እንደማይታይ በማሳወቅ ነበር።
በ2009 ጠ/ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ “መሰዋት” በስተቀር ኢህአዴግ አንዳችም ለውጥ ባላደረገበት ሁኔታ ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 19፤2006 (March 19፤2014) ይኸው እውቅና ሰጪ ተቋም የራሱን ውሳኔ ቀልብሶ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ከውሳኔው ቀናት በፊት በጓሮ የሚወጠን ድርጊት እንዳለ መረጃ ደርሶት የማሳሰቢያ ተቃውሞ ያሰራጨው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘውየሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እንዳለው ከሆነ ከተገለበጠው ውሳኔ በስተጀርባ ሚስ ክሌር ሾርት ከፊት ረድፍ ተቀምጠዋል።
ማመልከቻው እንደገና እንዲታይና የቦርዱ የቀድሞ ውሳኔ እንዲገለብጥ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የቀድሞ የእንግሊዝ ዓለምአቀፍ ትብብር ሚ/ር የሆኑት ክሌር ሾርት መሆናቸውን የድርጅቱ መግለጫው ይፋ አድርጓል። እኚህ ግለሰብ የአፍሪካ አምባገነኖችን በመደገፍ የሚታወቁ ሲሆን ይህ ከጥቅማቸው ጋር የተሳሰረው ግንኙነታቸው አሁንም ኢህአዴግን እንዲደግፉ እንዳደረጋቸው ይነገራል፡፡ እንዲሁም በሌሎች ኢህአዴግ ባቋቋማቸው ዓለምአቀፋዊነት ሽፋን በተላበሱ ድርጅቶች ውስጥ የአመራር አባል በመሆን ሚስ ሾርት እንደሚያገለግሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የእንግሊዝ ፓርላማ አባል በነበሩበት ወቅትም ያላወጡትን ወጪ አውጥቻለሁ በማለት በብዙ ሺዎች የሚገመት ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ መሆናቸው በወቅቱ ዴይሊ ቴሌግራፍ ባወጣው መረጃ አጋልጦ ነበር፡፡ የተወሰነውን ገንዘብ የመለሱ ቢሆንም ጋዜጣው በወቅቱ ያወጣው መረጃ ግለሰቧ የሕዝብን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው የተጠቀሙ “ሙሰኛ” መሆናቸውን ያስረዳል፡፡
ክሌር ሾርት
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንደሚሉት ከሆነ ባለፈው ረቡዕ ኦስሎ፤ ኖርዌይ ላይ ውሳኔው በተላለፈበት ወቅት ሚስ ሾርት በግልጽ የኢህአዴግ ደጋፊ በመሆን ተጽዕኖ በማድረግ ወደ ውሳኔ እንዲደረስ ግፊት አድርገዋል፡፡ ግለሰቧ ባላቸው ኃላፊነት በመጠቀም (የEITI የቦርድ ኃላፊ ናቸው) እንዲህ ዓይነቱ ግልጽና ወገናዊነት የታየበት ድጋፍ በማድረግ ከድርጅቱ አሠራር ውጪ ውሳኔ እንዲሰጥ ማድረጋቸው ለወደፊት በሚቀርቡ ማመልከቻዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የአሠራር ችግር እንደሚያስከትል ካሁኑ እየተጠቆመ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ከማዕድን ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ ማህበራዊ ቀውስ የደረሰባቸው አካባቢዎች እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት አካባቢዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ባልጸዳ የሽያጭ ሂደት ሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ የገዙት ሻኪሶ የወርቅ ማዕድን በህዝብ ላይ እያደረሰ ችግር የሚዘገንን ነው። በየጊዜው ግልጽ ባልሆነ የማስፋፊያ ውል የሚፈናቀሉና ከፋብሪካው በሚወጣው ዝቃጭ ለከፍተኛ ብክለት የተጋለጡ ዜጎች ድምጻቸውን ሲያሰሙ መታሰራቸው፣ መገረፋቸው፣ ለይስሙላ በተቋቋሙ ፍርድ ቤቶች የተፈረደባቸው እንዳሉ ታዛቢዎች ያስታውሳሉ።
በጋምቤላ ኢንቨስትመንት ህዝብን እየበላ እንደሆነ የሚጠቁሙት ክፍሎች “ኢንቨስትመንት በከፍተኛ ደረጃ የሚደገፍና የሚበረታታ ተግባር ቢሆንም፣ ኢህአዴግ ፍትሃዊ በሆነ ደረጃ መጠቀም፣ ማስተዳደር፣ መምራትና ኢንቨስትመንቱን ህዝብ “የኔ” ብሎ በመቀበል እንክብካቤ እንዲያደርግ የሚያስችል ስርዓት አለማበጀቱን እንደ ዋንኛ ችግር ያነሳሉ። ኢህአዴግን ያዘጋጀው ህወሃት በራሱ ሰዎች አማካይነት ከውጪ ሰዎች ጋር እየተሻረከ ለህዝብ ጥቅም ሊውል የሚገባውን ሃብት ወደ ውስን ቋት እንደሚያግዝ የሚገልጹት እነዚሁ ክፍሎች” ይህ ዓለም የሚያውቀውን፣ ራሳቸው ህወሃቶችም የማይክዱትን እውነት ነው ብለዋል። ዜጎች የአገራቸው ሃብት ተጠቃሚ ከመሆን ይልቅ አካባቢያቸው ባደላቸው የተፈጥሮ ሃብት ሳቢያ መከራ ሲደርስባቸው፣ ሲሰቃዩ፣ ሲገረፉና፣ ሲገደሉ ማየት በተለመደባት ኢትዮጵያ ውስጥ ለኢህአዴግ የማይገባውን ካባ መደረብ ውሎ አድሮ የሚጋለጥ ክፉ ተግባር እንደሆነም አመልክተዋል።
አነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙና ኢህአዴግ “ልማታዊ” የሚላቸው ኢንቨስተሮች ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ የሚመደብ መዋዕለ ንዋይ የሚያፈሱ ባለሃብቶች ኢንቨስት የሚያደርጉበትን አገር ለመምረጥ የመጀመሪያው መለያቸው የEITI ድረገጽ የአባል አገራት ዝርዝር እንደሆነ ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ኢህአዴግም አስፈላጊውን የምዝገባና የማመልከቻ መስፈርት በማሟላት የተቋሙን እውቅና የጠየቀው በድርጅቱ ድረገጽ ላይ ለመመዝገብ ነበር። የሁለት ጊዜ ሙከራው ቢከሽፋም በመጨረሻ ተሳክቶለታል። ስኬቱንና የስኬቱን መንገድ፣ በተለይም የዳይሬክተሯ ክሌር ሾርት ጉዳይና የተዘጋውን ፋይል በማንሳት ውሳኔው የተገለበጠበት አካሄድ ኦስሎ በሚገኘው ሃያ የቦርድ አባላት ባሉበት ተቋም ውስጥም ግራ ያጋባቸው እንዳሉ መረጃዎች አሉ።
ኢህአዴግ አጓድለሃል ተብሎ የሚከሰስባቸውን የዴሞክራሲ ግባቶችና የሰው ልጆች የተፈጥሮ መብቶች፣ አንዲሆም አፋኝ የተባሉትን ህጎች አጠናክሮ ተግባር ላይ ባዋለበት ሁኔታ፣ የዚሁ የአፈናው ሰለባዎች በተለያዩ ማጎሪያዎች ውስጥ ሆነው ድምጻቸውን በሚያስተጋቡበት ወቅት፣ EITI ከተቋቋመበት ዓላማና “መሰረቴ” ከሚለው የግልጽነትና ተጠያቂነት መርህ በተጻራሪ ግልጽነትና ተጠያቂነት በጎደለው መልኩ ለኢህአዴግ የደረበው ብሉኮ ጉዳይ እየተመረመረ አንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ጉዳዩን የሚከታተሉ “ግልጽነትና ተጠያቂነት በኦስሎ ተፈረደባቸው” ሲሉ ምጸት ሰጥተዋል፤ የክሌር ሾርትንም አካሄድ በEITI የህወሃት/ኢህአዴግ ተወካይ በማለት ተችተዋል። ይህንኑ ጉዳይ እመልክቶ ከሳምንት በፊት ለሪፖርተር አጭር መልስ የሰጡት የማዕድን ሚኒስትሩ EITI ውሳኔውን ያነሳል የሚል ጥርጣሬ እንዳለባቸው የሚያሳብቅባቸው መልስ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ዳያስፖራው እንደሚገባው አለመንቀሳቀሱ እንደ ሽንፈትና አቅጣጫ መሳት እንደሚቆጠር ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ጠቁመዋል፡፡ ዳያስፖራው ከጥቃቅንና ስሜታዊ ጉዳዮች በማለፍ በከፍተኛና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የማድረግ አመለካከቱን ማስፋት እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ አለበለዚያ ኢህአዴግ እንደዚህ ዓይነቱን አጋጣሚ በመጠቀም የራሱን ገጽታ በዓለምአቀፍ መድረኮች እየወለወለ በማቅረብ የሥልጣን ዘመኑን እንደሚያራዝም ጠቁመዋል፡፡

Saturday, March 22, 2014

(ሰበር ዜና) ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ከሀገር እንዳይወጣ በኢሚግሬሽን ታገተ

ሰማያዊ ፓርቲ እንዳስታወቀው በአሜሪካን ሀገር ስቴት ዲፓርትመንት የተዘጋጀለትን ወጣት የአፍሪካ መሪ የሚል ሽልማት ለመውሰድ ዛሬ ሌሊት ወደ አሜሪካ ያቀና የነበረው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በቦሌ አየር መንገድ ከተገኘ በኋላ ከሀገር መውጣት አትችልም በሚል ታግቶ ይገኛል፡፡ በረራው 4 ሰአት ላይ የነበረ ሲሆን እስካሁን እስከሌሊቱ 8 ሰኣት ድረስ ታግቶ ይገኛል፡፡
ዝርዝር መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን።

Wednesday, March 19, 2014

US slams Ethiopia’s human rights abuse

(OPride) — The United States in a scathing report on Thursday accused Ethiopia of curtailing freedom of expression and association, using politically motivated trials, harassment and intimidation of activists and journalists.
ImageEthiopia holds estimated 70,000-80,000 persons, including some 2,500 women and nearly 600 children incarcerated with their mothers, in severely overcrowded six federal and 120 regional prisons, the U.S. said in its voluminous 2013 Human Rights Reportreleased by Secretary of State John Kerry. “There also were many unofficial detention centers throughout the country, including in Dedessa, Bir Sheleko, Tolay, Hormat, Blate, Tatek, Jijiga, Holeta, and Senkele,” the report said. 
While it said pretrial detention in local police stations were marred with poor hygiene and police abuse, the report also highlighted impunity for security forces who often commit politically-motivated killings against dissidents and opposition party members as “a serious problem.” The Ethiopian government rarely, if ever, took actions “to prosecute or otherwise punish officials who committed abuses other than corruption,” the report added.
The report named some of the well-known political prisoners and journalists including Eskinder Nega, Bekele Gerba, Olbana Lelisa, Reeyot Alemu and Woubeshet Taye.“Federal Supreme Court upheld the 2012 convictions under the criminal code of Bekele Gerba and Olbana Lelisa, two well-known political opposition figures from the Oromo ethnic group, for conspiracy to overthrow the government and conspiracy to incite unrest,” the report noted.

“The Supreme Court subsequently determined the Federal High Court did not consider mitigating circumstances and reduced Bekele’s sentence from eight years to three years and seven months. The Supreme Court also reduced Olbana’s sentenced from 13 to 11 years. Courts convicted 69 members of Oromo political opposition parties, charged separately in 2011 under the criminal code with “attacking the political or territorial integrity of the state.”
Gerba, who has fully served out his reduced time, was widely expected to be released last month. However, according to family sources, prison officials gave conflicting reasons for his continued imprisonment, including that his time at the Maekelawi prison doesn’t count or his file was misplaced. Meanwhile, both Gerba and Lelisa are reportedly ill with restricted and limited medical care. 
Terminally ill
Lelisa is a longtime Oromo rights activist with Oromo Peoples Congress (OPC), who rose through the ranks of the organization from a sole member to top leadership. He competed in the last three elections representing the Caliya district in West Shewa. He was elected to the Oromia regional parliament in 2005. He was subsequently arrested on concocted charges of plotting to overthrow government by working with the Oromo Liberation Front (OLF), recruiting youth for armed rebellion and for inciting the frequent youth revolt in Ambo and West Shewa. 
Lelisa, who has so far served three years of the 11 years sentence, reports being mistreated while in prison. He has repeatedly been beaten by unidentified men at Kaliti prison with orders from security services. He has sustained serious wounds from the beatings by government agents who pose as prisoners, according to OPride sources. Lelisa, who is terminally ill and said to be on a long-term medication for undisclosed condition, had repeatedly appealed to the higher court about his mistreatment but received no response to date. 
Singling out the Oromo
While the State Department’s report is short on details, there are several evidences that show the Ethiopian government continues to single out Oromo dissidents. Last year, the OLF released a partial list (independently verified by a reputable OPride source) of 528 individuals sentenced to death and life imprisonment on purely political grounds.
The list includes names of individuals, their gender, and ethnic backgrounds. Underscoring the disproportionate repression of the Oromo, of the 528 individuals who were sentenced to death or life imprisonment by the Ethiopian courts, 459 are Oromo nationals followed by 52 Amhara nationals. “This list clearly indicates that the minority regime in Ethiopia is using its kangaroo courts for destroying Oromo and Amhara nationals who are viewed as potential threat to the regimes hold on to power,” one informant, who asked not to be named, told OPride.
As documented by various international human rights organizations, today, it is a serious crime, under the Tigrean dominated Ethiopian government to support any independent Oromo organization. Thousands of Oromos have been imprisoned, tortured and killed extra-judicially for no apparent reason other than expressing Oromo national feeling and for their support of Oromo organizations such as the OLF.
The selective and systematic targeting of Oromo in Ethiopia by the current began in 1992 when the OLF which jointly ruled Ethiopia from 1991-1992  with the Tigrayan Liberation Front (TPLF) was banned and its members and supporters jailed for years and hundreds executed without due process of law. Although Oromia, the Oromo regional state in Ethiopia, is autonomous in name, the Oromo do not have any meaningful voice in the affairs of their own state, which is totally controlled by the TPLF.
The later represents no more than seven percent of the population of Ethiopia, while the Oromo, who constitute the single largest national group in Ethiopia and the third largest national group in the whole of Africa. The Oromo are denied the basic democratic rights to organize freely and legally and express their political opinions. There is no single independent newspaper or media outlet catering to the Oromo populace in their native tongue.
The TPLF fears the Oromo numerical strength deliberately characterizes all independent Oromo organizations, which it does not control as the “terror wing” of the OLF.  The goal for such characterization is to persecute peaceful supporters of the OLF behind the façade of fighting against a “ terrorist organization.” Under the anti-terror law of the current Ethiopian regime, anyone who is suspected of peacefully supporting the OLF, could be sentenced to life imprisonment or executed. The above mentioned 459 Oromo nationals who were sentenced to death or life imprisonment are all  suspected OLF supporters.

Destroying the lives of 528 innocent human beings on political ground is a crime against humanity, which must be condemned by all civilized nations. The tearless cry of the U.S. AnnuaL Human Rights report notwithstanding, at this moment no calling is more urgent and more noble and no responsibility greater for those who believe in human rights than raising their voice for pressuring the government of Ethiopia to free the 528 innocent individuals who were sentenced to death and life imprisonment  on purely political grounds.
In the last year alone, two Oromo activists have died in prison under mysterious circumnances. Last year, OPride reported about the death in prison of former UNHCR recognized refugee, engineer Tesfahun Chemeda. Last month, a former parliamentary candidate from Chalenqo in Western Hararghe, Ahmed Nejash died in prison. According to an OPC source, Nejash successfully run and challenegd Sufian Ahmed, Ethiopia’s Minister of Finance and Development, during the 2010 elections. He was subsequently arrested in 2011 alleged of being an OLF activist. Although his death recieved scant media coverage even within the Oromo community, a close relative of the late Jarra Abba Gadaa, Nejash is one of the veterans of Oromo people’s struggle. “He was sentenced to seven years, which was also upheld by the higher court,” the OPC source told OPride. “He was in Zuway with Bekele and Olbana and he was healthy the last time I saw him in 2013.”
source:- http://www.opride.com/oromsis/news/horn-of-africa/3735-us-slams-ethiopia-s-human-rights-abuse

Wednesday, March 12, 2014

የኢትዮጵያ ጦር በአልሸባብ ላይ የተጠናከረ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ የንቅናቄው መሪ በኢትዮጵያ ላይ ጅሃድ አወጁ

ኢሳት ዜና :-የአልሸባብ መሪ አህመድ ጎዳኔ በቅጽል ስማቸው ሙክታር አቡ አል ዙቢያር ” ለአሜሪካ መንግስት ጥቅም የሚዋጉት የሞቃዲሾ መንግስትና የኢትዮጵያ ጦር በጦርነቱ ድል ይሆናሉ “ብለዋል።
“ሶማሊዎች ሃይማኖታችሁ ተደፍሯል፣ መሬታችሁ ተከፋፍሏል፣ ንብረታችሁ ተዘርፏል፣ ድላችን በጅሃድ ላይ የተመሰረተ ነው ” ሲሉ ሚ/ር ጎዳኔ ተናግረዋል።
ወደብ አልባ የሆነችው ኢትዮጵያ ወደብ ለማገኘት ስትል ሶማሊያን መውረሩዋን የሚናገሩት የአልሸባቡ መሪ ፣ “ኢትዮጵያ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ ትሸነፋለች፣ ሙስሊሞችም ተጠናክረው ይወጣሉ። ብለዋል።
ኢትዮጵያና ኬንያ የሶማሊያ ግዛቶችን ለመከፋፈል ማቀዳቸውንም መሪው አክለዋል። አምና በአልሸባብ ውስጥ የተፈጠረውን የውስጥ ሽኩቻ ተከትሎ በርካታ የድርጀቱ መሪዎች ስልጣናቸውን ለቀዋል ወይም ተገድለዋል።
አልሸባብ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በህዝቡ ላይ የሚፈጽመው የሽብር ጥቃት ብዙ ሶማሊዎችን ሳያሳዝን አልቀረም። አህመድ ጎዳኔ ያስተላለፉት አዲሱ ጥሪ ከዚህ በፊት ጣህር አዌይስ እንዳስተላለፉት የብዙ ሶማሊዎችን ስሜት ይገዛል ተብሎ አይጠበቅም።
የኢትዮጵያ ጦር እየሰነዘረ ባለው ጥቃት ጠንካራ የሚባሉ የአልሸባብ ይዞታዎች እየተለቀቁ ነው። የአትዮጵያ ጦር በመላዋ ሶማሊያ ከሚገኘውን አልሸባብ ጋር የመዋጋት ፍላጎት ይኑረው አይኑረው አልታወቀም።

Sunday, March 9, 2014

ሰበር ዜና ለነጻነት የሮጡት ታሰሩ ዛሬ በተካሄደው የሴቶች 5ሺሜትር ሩጫ ላይ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ‹‹ለነጻነት እንሩጥ›› በሚል መሪ ቃል የተለያዩ ፖለቲካዊ ጥያቄዎችን በማንሳት ተሳታፊውን ሲያነቃቁ ውለዋል፡፡ በሩጫው ላይ ከተነሱ ጥያቄዎችና መፈክሮች መካከል ርዕዮትና ሌሎች የህሌና እስረኞች ይፈቱ፣ መብትን መጠየቅ አሸባሪነት ከሆነ አሸባሪዎች ነን፣ ውሃ ናፈቀን፣ መብራት ናፈቀን፣ ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ዴሞክራሲ፣ ውሸት ሰለቸንና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡ ከመነሻው የጀመረው የተቃውሞ ድምጽ እስከ ማብቂያው የቀጠለ ሲሆን ሲከታተሏቸው የዋት ፖሊስና የደህንነት ኃይሎች ሩጫውን ጨርሰው ሲገቡ አስረዋቸዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የሩጫው ተሳታፊዎች ታስረው ይገኛሉ፡

ETHIOPIAN FEDERAL POLICE ARRESTS BLUE PARTY'S WOMEN ADDIS ABABA 09/03/2014


Girum Zeleke's photo.

Today's 5000 meter running event ended dramatically. 
In a major show of force, dozens of Addis Ababa police officers in riot gear arrested the Blue Party Women Groups who were shouting that political prisoners must be released. These young women were demanding for the release of journalists and political prisoners. 

The women were shouting “Release Reeyot Alemu!!” .. “Release the Journalists!!”… “Release all political prisoners!!”
The police arrested dozens of these women who all are members of the Blue Party. Some of these are members of the Executive Committee of the Blue Party. The names of the arrestee and their condition will be announced on the internet media and on the international news channels in short time.

Friday, March 7, 2014

ሰበር ዜና: የአዲስ አበባው ሲኖዶስ የአቡነ ጳውሎስ ሐውልት እንዲፈርስ ወሰነ




ሲኖዶሱ ቦሌ መድኃኔ ዓለም የቆመው የፓትርያርኩ ሐውልት እንዲፈርስ፣ በየቤተ ክርስቲያኑ የተሰቀለው የፓትርያርኩ ፎቶም እንዲወርድ ዛሬ ጠዋት ወሰኗል፡፡ እንዴት እዚህ ውሳኔ ላይ ሲኖዶሱ እንደደረሰ በዝርዝር የቀረበ ማብራሪያ ይፋ አልሆነም::

ይህ መልካም ጅምር ይመስላል:: መንግሥተ ሰማያቱ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ ብሎ የተናገረውን ሰው ዓይነት መሆኑ ነው መሰለኝ:: የአዲስ አበባው ሲኖዶስ ቅዱስነቱ ቀርቶበት በጸጸት እንዲህ ደህናና የአምላክን መስመር ለመያዝ መፈለጉ ጥሩ ጅምር ነው ካዘለቀው:: የአዲስ አበባው ሲኖዶስ የፖለቲካ መሣሪያነቱን ቀነስ አርጎ የእግዚአብሄርን ቃል መከተሉ እሰየው የሚያስኝ ነው::

የአዲስ አበባው ሲኖዶስ ወደ ልቡ እየተመለሰ ይሆን? የወደፊቱን ደግሞ እንናያለን::

ብልጡ አልጀዚራ ኢቲቪን ሸወደው


ከበደ ካሳ
በኳታር መንግስት ሃብት የተቋቋመውና ስነ አፈጣጠሩ ሲጠናም የምዕራቡን አለምና የእስራኤል ሚዲያን የአረብ ሀገራት ጉዳይ አዘጋገብ ለመገዳደር የተፈጠረው የአልጀዚራ ቴሌቪዥን ጣቢያ ስትራግል ኦቨር ናይል በሚል ርዕስ አንድ ዘጋቢ ፊልም አዘጋጅቶ ነበር። ጣቢያው ይህን ፊልም በቴሌቪዥኑ ያስተላለፈው ሲሆን በድረ ገፁ ላይ ስለጫነውም በርካቶች ተመልክተውታል።
የዘጋቢ ፊልሙ ይዘት በናይል ወንዝ የተነሳ በላይኛውና በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት መካከል ስለነገሰ ውጥረት ሲሆን ትኩረት ያደረገው ደግሞ ከላይኛው ተፋሰስ ኢትዮጵያ ላይ፤ ከታችኛው ተፋሰስ ደግሞ ግብፅ ላይ ነው። ይህን ፊልም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከሞላ ጎደል እንደወረደ በሚባል ደረጃ ወደ አማርኛ ተርጉሞ አቅርቦታል። ‘ጠብቁን’ የሚል ማስታወቂያ መሰራቱና ፊልሙ በተደጋጋሚ መታየቱ የአባይ ፍጥጫ ከሚለው ጩኸታም ርዕሱ ጋር ተዳምሮ በርካታ ኢትዮጵያዊያን እንደተከታተሉት ለመገመት አይከብድም።
ይህን ዘጋቢ ፊልም የተከታተሉ የምቀርባቸውን ሰዎች ስለ ዘገባው ያላቸውን አስተያየት ጠይቄያቸው ነበር። የሚበዙቱ እንዳደነቁት ነግረውኛል። ሁሉም ለማለት በሚቻልበት ደረጃ በምስል አጠቃቀሙ፤ በትረካው ፍሰትና በታሪክ አወቃቀሩ በጥቅሉ በአቀራረብ ደረጃ ምርጥ የሚባል ዘጋቢ ፊልም እንደሆነ ይስማማሉ። እኔም በዚህ ረገድ ልዩነት የለኝም። ሆኖም አንዳንድ ያሳሰቡኝን ጥያቄዎች ሳነሳ የጠየቅኋቸውም እንደኔው ግር ይላቸዋል አለያም “እውነትክን ነው፤ ከኢትዮጵያ ጥቅምና አቋም ጋር ይጋጫል”ይሉኛል።
በእኔ እምነት ዘገባው ከኢትዮጵያ ይልቅ ለግብፅ ጥቅም ያደላ፤ ሶስተኛ ወገን ለኢትዮጵያ ሳይሆን ለግብፅ እንዲጨነቅላት/እንዲያዝንላት የሚያደርግና ኢትዮጵያ ከምትከተለው አብሮ የመልማት ወይም በጋራ የመጠቀም እሳቤ ይልቅ ለፍጥጫና ግጭት መንስዔነት የቀረበ ነው። ይህን የምለው አልጀዚራ የአረብ አለም ሚዲያ ነው፤ ግብፅ ደግሞ የአረቡ አለም እምብርት ነች ከሚል አጠቃላይ ፍረጃ ተነስቼ ሳይሆን ከራሱ ከዘገባው ይዘት በመነሳት ነው። የማነሳቸው መከራከሪያዎችም በፊልሙ ውስጥ ቃል በቃል የሰፈሩ ናቸው።
ይህ ዘጋቢ ፊልም ለኢትዮጵያ አይበጅም ስል ምክንያት ከማደርጋቸው አንዱ የአባይ/ናይል ወንዝ ከኢትዮጵያ ይልቅ ለግብፅ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ አድርጎ ማቅረቡ ነው። እንደ ፊልሙ አባይ ለግብፅ የህልውና ጉዳይ ሲሆን ለኢትዮጵያ ግን የልማት ወይም የእድገት ጉዳይ ነው። በዘገባው ላይ እንደተገለፀው ካይሮ የተፈጠረችውና ያደገችው በናይል ወንዝ የተነሳ ነው። ያለ ናይል አካባቢው ሰው ሊኖርበት የማይችል በረሃ ነው። ማንኛውም ግብፃዊ በወንዙ ዙሪያ የመስፈር ፍቅሩም ከፍተኛ ነው። ስለሆነም “ሄሮዲተስ ግብፅን የአባይ ስጦታ ብሎ ገልጧታል። ትክክለኛ አገላለፅ ነው” ሲል ይደመድማል።
“በ1959ኙ ስምምነት መሰረት ግብፅ ከአባይ ወንዝ 55.5 ቢሊዮን ሜትሪክ ኪውብ ውሃ ይደርሳታል። ሆኖም ግን ከዚያን ግዜ ጀምሮ የግብፅ ህዝብ በሶስት እጥፍ አድጎ 80 ሚሊዮን በመድረሱ የውሃ እጥረት አጋጥሟታል።” ተብሏል በፊልሙ ውስጥ። ቃለ ምልልሱ ያካተታቸው የግብፅ ወታደራዊ ተንታኝ “በህልውናና በደህንነት መካከል ልዩነት አለ፤ እኛ ሙሉ በሙሉ የአባይ ዉሃ ጥገኞች ነን። ሌላ የዉሃ ምንጭ የለንም። ስለዚህ ሃቁ ያለው በአባይ ዉሃ ላይ ስጋት የሚፈጥር ነገር ሲኖር በግብፆች ህልውና ላይ ያነጣጠረ ነው ማለት ነው። ይህ ደግሞ በእኛ ላይ የዉሃ ጥምና የሞት አደጋን እንዳያስከትል ያሰጋናል” ይላሉ።ስለተጠቃሚነት የተጠየቁት ኢትዮጵያዊ ወ/ሮ አጀበች ደግሞ በመብራት እጦት መሰቃየታቸውን ይናገራሉ። የነዚህ ንግግሮች ድምር አባይ/ናይል ለግብፃዉያን የህይወት ምንጭ፤ ለኢትዮጵያዉያን ግን የመብራት ምንጭ ነው የሚል ነው።
እኔ ወንዙ ለግብፅ በምን ያህል ደረጃ ያስፈልጋታል? የሚል ክርክር ውስጥ መግባት አልፈልግም። ወንዙ ከነሱ ህልውና ጋር አይተሳሰርም ብዬም አልከራከርም። ከግብፅ በላይ ለእኛ ያስፈልገናልም አልልም። ግን ሶስት ጥያቄዎችን አነሳለሁ።
አንደኛው ናይል ለግብፆች የሞት የሽረት ጉዳይ ስለመሆኑ ማውራቱ ለኢቲቪ ምን ይፈይድለታል? የሚል ነው። ይህንንማ ግብፃውያን ከውልደት እስከሞታቸው የሚሰበኩት አይደለም እንዴ። ይህንንማ በራሳቸው ሚዲያ ሁሌ የሚደጋግሙልን አይደል እንዴ? ትክክል አለመሆናቸውን ለማሳየት ነው እንዳልል እንዲያ የሚል ነገር አልሰማሁበትም።
ሁለተኛው ጥያቄዬ ምን የሚያሰጋ ነገር ስለመጣ ነው የግብፆችን ስጋት ማንፀባረቅ ያስፈለገበት? የሚል ነው። ኢትዮጵያ የዉሃው መጠን አይቀንስም፤ ማንም ሳይጎዳ ወንዙን በጋራ መጠቀም እንችላለን እያለች ባለችበት ሁኔታ የነሱን “በዉሃ ጥም እናልቃለን” ስጋት ማውራት ‘እንትን ያለበት ዝላይ አይችልም‘ እንደሚባለው አያስመስልምን? ይህ ነገር በተለይ ኢትዮጵያና ብሪታኒያ ወንዙን ግብፅን ለማንበርከክ ይጠቀሙበት ነበር ተብሎ ከቀረበው ታሪክ ጋር ሲዳመር የግብፅ ስጋት ተገቢ ነው ወደሚል ማደማደሚያ አያደርስም? በፊልሙ ውስጥ ቀደምት የኢትዮጵያ ገዢዎች ከግብፅ ወርቅ ለማግኘት ሲሉ አባይን እንገድበዋለን እያሉ ያስፈራሩ እንደነበርና ብሪታኒያም የግብፆችን የፀረ ቅኝ ግዛት እንቅስቃሴ ለመግታት ስትል በጥቁር አባይና በነጭ አባይ መካከል ግድብ መስራቷ ተመልክቷል። አልጀዚራ በተዘዋዋሪ እየተናገረ ያለው አሁንም ኢትዮጵያ ግድቡን ግብፅን ለማንበርከክ ልትጠቀምበት ትችላለች ነው።
ሶስተኛው ጥያቄዬ ሁለቱ ሀገሮች በፍትሃዊ አጠቃቀም ላይ ስምምነት ባልደረሱበት ሁኔታ ይህን ፊልም ያየ ሶስተኛ ወገን ምን ሊያስብ ይችላል? ነው። በፊልሙ ላይ ግብፆች ገና ከአሁኑ በዉሃ እጥረት እየተሰቃዩ እንደሆነ ለማሳየት ታስቦ የገቡ ምስሎች ብዙ ናቸው። በርካታ ግብፃውያን ጀሪካኖችን ይዘው በአንድ ቧንቧ ዙሪያ ሲራኮቱ ይታያሉ። ይህ ግን አጠቃላዩን የግብፅ ሁኔታ ገላጭ አይደለም። ይልቁንም ግብፆች የሚታወቁትና ራሳቸውም የማይክዱት በዉሃ አጠቃቀማቸው አባካኝ እንደሆኑ ነው። እንግዲህ ሶስተኛ ወገን ሲባል ለጋሽ ድርጅቶችን፤ ሃያላን መንግስታትን፤ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትን ያካትታል። ይህን ፊልም ሲመለከቱ የሚያዝኑት ለማን ይሆናል? መብራት ለምትፈልገውና ሌሎች አማራጮች አሏት ተብላ በፊልሙ ለተፈረጀችው ኢትዮጵያ? ወይስ ህይወቷ በሙሉ በናይል ላይ የተንጠለጠለና የመጠጥ ዉሃ አጥታ የምትሰቃይ ተደርጋ ለተሳለችው ግብፅ?
ሁለተኛው የመከራከሪያ ነጥቤ ዘጋቢ ፊልሙ አባይ/ናይልን ከትብብር ይልቅ የግጭት ምንጭ አድርጎ ስሎታል የሚል ነው። ይህን የምመዝነው ኢትዮጵያ ከያዘችው አባይ/ናይል የትብብር እንጂ የግጭት ምንጭ ሊሆን አይችልም ከሚለው አቋም ተነስቼ ነው። የዘጋቢ ፊልሙ ርዕስ በእንግሊዘኛው ስትራግል ኦቨር ናይል የሚል ሲሆን ኢቲቪ የተረጎመውም የአባይ ፍጥጫ በሚል ነው። የፊልሙ ችግር ከዚህ ይነሳል። የአልጀዚራን ቀልብ የሳበው ኢትዮጵያ የምትከተለው አባይ/ናይል ለሁላችንም በቂ ነው የሚለው የትብብር መንፈስ ሳይሆን ግብፅ የምትሰብከው የዜሮ ድምር ውጤት ነው። በግልፅም “ናይል የህይወትም የግጭትም ምንጭ ነው” ይላል። የህይወት ምንጭ የተባለው ለግብፅ ሲሆን የግጭት ምንጭ የተባለው ለሁለቱ ሀገራት መሆኑ ነው። የትብብር ምንጭ መሆን እንደሚችል ግን አያረጋግጥም።
ኢትዮጵያና ግብፅ ያላቸው ባላንጣነት እድሜ ጠገብ መሆኑን የሚገልፀው ይህ ፊልም ሁለቱም ሀገራት የስልጣኔ ምንጭ ከሆኑበት የጥንቱ ታሪካቸው ጀምሮ ተቀናቃኝ ሆነው መኖራቸውን ያሳያል። አፄ ኃይለስላሴ እና ገማል አብደል ናስር ሁለቱም ራሳቸውን የአፍሪካ ግንባር ቀደም መሪ አድርገው ስለሚወስዱ በያዟቸው ተቃራኒ የፖለቲካ አስተሳሰብ ልዩነት /ኢምፔሪያሊስትና ፀረ ኢምፔሪያሊስት/ ውስጥ ሆነው በተቀናቃኝነት መኖራቸውን ያትታል። ውጥረቱ በደርግ መንግስት ወቅትም መቀጠሉንና የዚህም ምንጩ መንግስቱ ኃይለማርያም ፊቱን ወደ ሶቪየት ሲያዞር አንዋር ሳዳት ደግሞ ወደ ምዕራባውያን በማዞሩ ሁለቱ ሀገሮች በሁለቱ የአለም ጎራዎች ማዶና ማዶ መሰለፋቸው እንደሆነ ያስታውሳል። አሁን ደግሞ ኢትዮጵያ አስቸጋሪ ፈተና ውስጥ ገብታለች ይላል የአልጀዚራው ጋዜጠኛ።እንደዘገባው “አሁን ኢትዮጵያ በሁለት አማራጮች የተወጠረች ሀገር ሆናለች። በአንድ በኩል ወንዙን ለልማት የማዋል በሌላ በኩል ደግሞ ከታችኞቹ የአባይ ተፋሰስ ጎረቤቶቿ ጋር ያላትን ግንኙነት በማሻከር መካከል ያሉትን አማራጮች በትኩረት ታያቸዋለች።”
እዚህም ላይ ዘገባው እውነትን አልያዘም ብዬ አልከራከርም። ጥያቄዬ ይህ እውነት ትብብርን በምንሻው በእኛ በኢትዮጵያውያን መዘገቡ ፋይዳው ምንድን ነው? የሚል ነው። የኔ ጥያቄ ለምን ያለፉትን የግጭት መንስዔዎቻችንን ከምናጎላ አዳዲሶቹን የትብብር አማራጮቻችንን አንተነትንም? የሚል ነው። አሁን አፄዎቹ የሉም፤ ደርግም ተገርስሷል። በምትኩ ያለው‘በጠላቶች ተከብቤያለሁ’ ከሚል የቆየ ስሜት ራሱን አውጥቶ ከጎረቤቶቹ ጋር በጥቅም የተሳሰረ፤ ይህንንም ወደ ሌላ ታላቅ ምዕራፍ ለማሸጋገር እየሰራ ያለ መንግስት ነው። ታዲያ ፊልሙ ምነዋ ይህን ተግባራችንን ዘነጋው? ምነውስ ከጎረቤቶቻችን ጋር ያለንን ግንኙነት ሳናሻክር አብረን መበልፀግ ይቻላል የሚለውን ሶስተኛውን አማራጭ ሳያቀርበው አለፈ?
ወደ ሶስተኛው ምክንያቴ ልለፍ። በዚህ ዘጋቢ ፊልም ላይ የኢትዮጵያን ጥቅም የሚጎዱ ነገር ግን በአግባቡ ምላሽ ያልተሰጠባቸው ሃሳቦች አሉ። አንደኛው ግብፃዊው የፖለቲካ ተንታኝ አብዱል ዋሂብ ያነሱት ሃሳብ ነው። “የቀድሞ ስምምነቶችን ማክበር አለብን። ይህ ለአለም አቀፋዊ የሀገራት ድንበርም የሚያገለግል አካሄድ ነው። ለምሳሌ ከነፃነት በፊት የነበሩ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ድንበሮችን መቀየር አንችልም። እነዚህ በቅኝ ገዢዎች የተከለሉ ድንበሮች ከነፃነትም በኃላ ህጋዊ ሆነው እንዲያገለግሉ ከስምምነት ተደርሷል። ስለዚህ በአባይ ዉሃ አጠቃቀም ዙሪያ የተፈረሙትንም ስምምነቶች በተመሳሳይ መልኩ ማየት ነው።” ይላሉ። የ1929ኙን ስምምነት መሆኑ ነው። ጋዜጠኛው ደግሞ “የላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ግን እነኚህ ስምምነቶች የቅኝ ግዛት ቅሪት ስለሆኑ ተቀባይነት የላቸውም ሲሉ ይከራከራሉ” ይላል።
የኢትዮጵያ መከራከሪያ ግን ይህ ሊሆን አይችልም። የስምምነቱ አካል ስላልሆንኩ ለመቀበል የሚያስገድደኝ ምንም አይነት ህግ የለም ነው የምትለው ኢትዮጵያ። የቅኝ ግዛት ቅሪት በሚለው ከሆነማ አብዱል ዋሂብ እንዳሉት የድንበር ማካለሉን ተቀብለን ስምምነቶቹን እንቢ የምንልበት ምክንያት አይኖርም። አልጀዚራ ይህ ጠፍቶት ሳይሆን ኢትዮጵያ የያዘችውን ትክክለኛና ምክንያታዊ አቋም አለባብሶ ለማለፍ ስለፈለገ ነው።
በሌላ መልኩ “በአለም አቀፉ ህግ መሰረት የላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ግድብ ከመስራታቸው በፊት የታችኞቹን ተፋሰስ ሀገራት የማማከር ግዴታ ስላለባቸው ለግብፅ ማሳወቅ አለባቸው” ይላሉ። ይህም እንደ ሃቅ ተቀባይነት አግኝቶ ያለፈ ነው በዘጋቢ ፊልሙ። እውነታው ግን ይህን አይነት አስገዳጅ አለም አቀፍ ህግ ያለመኖሩ ነው። ይልቁንም ህጉ የሀገራትን ሉዓላዊ መብት የሚያከብርና ፍትሃዊና በሌላው ላይ ትርጉም ያለው ጉዳት ያለማድረስ መርሆችን የሚያበረታታ መሆኑ ነው።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በ1997 ያወጣው ለመጓጓዣነት የማያገለግሉ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች አጠቃቀም ስምምነት እኩል/ሚዛናዊ ተጠቃሚነትና ከፍተኛ ጉዳት ያለማድረስን ነው መሰረት የሚያደርገው። እኩል/ሚዛናዊ ተጠቃሚነት ደግሞ የህዝብ ብዛትን፤ የቆዳ ስፋትን፤ ሊታረስ የሚችል መሬትን፤ ሌሎች አማራጭ ምንጮችንና የዉሃውን ደህንነት መጠበቅ የሚባሉ ጉዳዮችን ያቀፈ ነው። ስትራግል ኦቨር ናይል ግን እነዚህን ጉዳዮች ዘወር ብሎ አላያቸውም።
ሌላው ግብፆች የሚመኩበትና እስካሁንም አወዛጋቢ የሆነው በአፄ ሚኒሊክና በብሪታኒያ መንግስት መካከል ተፈርሟል የሚባለው ስምምነት ነው። ይህንን የግብፆችን መከራከሪያ ነጥብ ሳያስተባብሉ እንደወረደ ከማቅረብ በላይ የኢቲቪን ወገንተኝነት ጥያቄ ውስጥ የሚከት ጉዳይ አይኖርም። ፊልሙ ላይ እንዲህ ይላል። እንግሊዝ እ.አ.አ በወርሃ ግንቦት 1902 ከአፄ ሚኒሊክ ጋር አንድ ስምምነት ተፈራረመች። በዚህ ስምምነት አፄ ሚኒሊክ የአባይ ወንዝ ወደ ግብፅ የሚያደርገውን ፍሰት የሚያሰናክል ወይም የዉሃውን መጠን የሚቀንስ ምንም አይነት ግድብ እንደማይገነቡ ቃል ገቡ።” የሚገርመው በቅርቡ በናይል ቲቪ በተካሄደ የቀጥታ ስርጭት ውይይት ላይም የቀድሞው የግብፅ የዉሃ ሚኒስትር ዶ/ር ናስር አደም ይችን ነጥብ አንስተዋታል።
አፄ ሚኒሊክ ፈርመውታል የተባለው ስምምነት ፕሮፌሰር አሊ አብዱላህ አሊ እንደሚሉት ቢያንስ በሁለት መሰረታዊ ነጥቦች የተነሳ በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የለውም። አንደኛ ስምምነቱን የሁለቱ ሀገራት የወቅቱ የዘውድ ም/ቤቶች አላፀደቁትም። ሁለተኛ የስምምነቱ የአማርኛና የእንግሊዝኛ ትርጉም ግጭት ፈጥሮ ስለነበር አፄ ሚኒሊክ በወቅቱ አልተቀበሉትም። አልጀዚራ ያዘጋጀውና ኢቲቪ የተቀበለው ዘጋቢ ፊልም ይህንን የግብፅን የክስ ነጥብ ያሳይና የኢትዮጵያን መከራከሪያ ነጥብ ግን አያስቀምጥም። በዚህም በህግ የመርታት አዝማሚያው ለግብፅ ያጋደለ እንዲመስል አድርጓል።
የመጨረሻውን ነጥቤን ላንሳ። እንደፊልሙ ከሆነ የኢትዮጵያን የአፈር ማዕድን ጠራርጎ የሚሄደው ደለል ለግብፃዊያን ሲሳያቸው ነው። ፊልሙ “ለም አፈር ለግብፃውያን ዋና ስጦታ ነው” ይልና ምክንያቱን ሲያብራራ መሬታቸው በለም አፈር ይበለፅግላቸውና አጥጋቢ ምርት ያገኛሉ ይላል። ይህን ከተቀበልን ኢትዮጵያ ‘ግድቤ ደለልን በመቀነስ የታችኞቹን ሀገራት ተጠቃሚ ያደርጋል’ የምትለው ድለላ /lip service/ ነው ማለት ነው። አልጀዚራ ይህን ይበል እንጂ እውነታው ግን እሱ አይደለም። ግብፅ የአስዋን ግድብን ከገነባች በኋላ ደለሉ በግድቡ የታችኛው ክፍል ላይ ስለሚተኛ ተጠቃሚ ሳይሆን ተጎጂ ነው የነበረችው። ስለዚህም የኢትዮጵያ አቋም ትክክል ተብሎ ነበር መወሰድ ያለበት።
ልብ በሉ፤ አሁን ልክ አይደለም የምለደው አልጀዚራን አይደለም፤ ኢቲቪን ነው። አልጀዚራማ ከሚዲያው ጥቅም ተነስቶ የሚፈልገውን መልዕክት አቅርቧል። እኔ የምተቸው የኢትዮጵያ የሆነውን ኢቲቪን ነው። ዘገባው ከላይ ያስቀመጥኳቸው የይዘት ጉድለቶች ሳሉበት ለምን ኢቲቪ አስተላለፈው? ነው የኔ ጥያቄ። ለአንድ ደቂቃ ማስታወቂያ በሺዎች የሚቆጠር ብር የሚቀበለው ኢቲቪ ለምን የአየር ሰዓቱን በዚህ ማቃጠል አስፈለገው? ነው የእኔ ጥያቄ። የኢትዮጵያን ጥቅም ማስጠበቅ የሚችል የፀዳ ዘጋቢ ፊልም በውስጡ ባለው የዶክመንታሪ ክፍል መስራት የሚችለው ኢቲቪ ለምን የአልጀዚራን ዥጉርጉር ፊልም መኮረጅ አስፈለገው? ነው የኔ ጥያቄ።
እያንዳንዱ ሚዲያ ሲቋቋም የራሱ ተልዕኮ ይዞ ነው። ለጥቅሙ የሚቆምለት ወገንም አለው። አልጀዚራ የኳታርን ብሔራዊ ጥቅም በሚጎዳ ተግባር ውስጥ እጁን አያስገባም። በአንፃሩ የኳታርን ሲያልፍ ደግሞ የአረቡን አለም አጀንዳዎች ከፍ ከፍ አድርጎ ያሰማል። ኢቲቪ የሚከተለው የሚዲያ ፍልስፍና ልማታዊ ጋዜጠኝነት ነው። በልማታዊ ዴሞክራሲ የፖለቲካ ኢኮኖሚ ውስጥ እንደመሆኑ በተለይ እንደ ኢቲቪ ያለ የህዝብ ሚዲያ ግልፅ ተልዕኮዎችን ይዞ መንቀሳቀሱ የማይቀር ነው። እናም የኢትዮጵያን ሕዳሴ ማብሰር ዋና ተልዕኮው ነው።
ሁለቱ ተቋሞች በተልዕኮም በሚከተሉት ፍልስፍናም የማይታረቁ ባህሪዎች አሏቸው። ኢቲቪ ከአልጀዚራ ያገኘውን ዘገባ እንደወረደ ለአድማጭ ተመልካቹ የሚዘረግፍ ከሆነ ተሸውዷል ማለት ነው። አሁንም የሚታየኝ ይሄው ነው። ግድ የላችሁም፤ አልጀዚራ በውብ ምስሎቹና በማራኪ አቀራረቡ የተነሳ ኢቲቪን ሸውዶታል። ግን ለሌላ ግዜ ትምህርት ይሆነዋል ብዬ አስባለሁ።

Thursday, March 6, 2014

ኢህአዴግ – ሌባ ወይስ አገር አስተዳዳሪ?ከላይ የጠየቅነው ጥያቄ ዛሬ የተነሳ አዲስ ነገር አይደለም። ኢህአዴግ መሰረቱን ዝርፊያ ላይ ያደረገ አገር አስተዳዳሪ መሆኑ ግብሩ ራሱ ምስክር ነውና “ሌባ አገር አስተዳዳሪ” ስለመሆኑ ማስተባበያ ሊያቀርብም አይቻለውም፤ አያስፈልገውም። ሌብነቱ አገርንና ህዝብን ወደ ገደል እየሰደደ መሆኑ ግን ሁሌም የሚያስጨንቅ ነውና ዛሬ እንደ አዲስ አነሳነው እንጂ!!

eprdf t or a


ከላይ የጠየቅነው ጥያቄ ዛሬ የተነሳ አዲስ ነገር አይደለም። ኢህአዴግ መሰረቱን ዝርፊያ ላይ ያደረገ አገር አስተዳዳሪ መሆኑ ግብሩ ራሱ ምስክር ነውና “ሌባ አገር አስተዳዳሪ” ስለመሆኑ ማስተባበያ ሊያቀርብም አይቻለውም፤ አያስፈልገውም። ሌብነቱ አገርንና ህዝብን ወደ ገደል እየሰደደ መሆኑ ግን ሁሌም የሚያስጨንቅ ነውና ዛሬ እንደ አዲስ አነሳነው እንጂ!!
ኢህአዴግ ግዙፍ፣ ሃብቱ በዶላር ካልሆነ በብር የማይቆጠር፣ በህገወጥ ንግድ ሰላማዊ ነጋዴዎችን የሚውጥ፣ ለብቻው መግቢያና መውጪያ የተዘጋጀለት፣ የተለየ ጨረታና የነጻ ቀረጥ እድል የሚበጅለት፣ በየትኛውም ተቋም እንደፈለገ መጋለብ የሚችል ልጓም አልባ የሆነ፣ በፈለገው ቦታና ማህበረሰብ ጥቅም ላይ እንዳሻው ከበሮ እየደለቀ የሚጨፍር፣ ጡሩምባ ይዞ የሚያንጠራባ፣ የፈለገውን ማስወገድ፣ ማሳገድ፣ ማስከፈት፣ ማዘጋት የሚችል፣ ድንበርና ኬላ የማይዘው የንግድ ተቋም አለው። እወክላቸዋለሁ በሚላቸው የአንድ ክልል ሕዝብ ስም ባቋቋመው ሻርክ ኦዲት በማያውቀው የ”ንግድ” ተቋም አማካይነት አገሪቷን እየዘረፈና እየዋጠ ነው።
አገሪቱ አምጣ የምታገኘውን የውጪ ምንዛሬ በበላይነት ሲፈልግ ከራሱ ባንክ፣ ሲያሻው የራሱ ሰዎች በሚያዙበት የህዝብ ባንኮች በተራ ትዕዛዝ ያግበሰብሳል። በፋይናንስ ዘርፉ ውስጥ እጅና እግሩን ነክሮ እንዳሻው ያንቦጫርቃል። የሚቀናቀኑ ብቅ ሲሉ እየበለተ ይሰቅላቸዋል። ሲያሻው ፋይል አስከፍቶ በ”አጎብዳጅ ባንዳ” ዳኞች ያስፈርድባቸዋል። “ጸረ ልማት” ብሎ የፍየል ወጠጤ ያዘፍንባቸዋል።
እንቶኔን ያየ … በሚል አገር ወዳዶች ሸሽተው አለቁ። ምሁሩ አገሩን ከዳ። ነጋዴው ኮበለለ። ወጣቱ በኑሮ ጠኔ መጨረሻው በማይታወቅ ስደት የባህር ላይ ሞትን መረጠ። የቻሉ አረብ ምድር ገብተው በግፍ አለንጋ ተጠበሱ። ኢኮኖሚያዊ ቀውሱ የበረታባቸው ራሳቸውን ማጥፋት ጀመሩ። ይህ ሁሉ የማያስደነግጣቸው ህወሃትና ጭፍሮቹ በጥጋብ ያገሳሉ።
ተቀናቃኞቹን በሰበብ ለማላመጥ የተቋቋመው የፌደራል የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ በሰጠው ማረጋገጫ ያለ ህጋዊ ቀረጥ ከሚነግዱ ድርጅቶች መካከል ይኸው የህወሃት ድርጅት ግንባር ቀደም ነው። ነገር ግን ጠያቂ የለውም። ለምን ቢባል ባለቤቱ ራሱ አገር መሪ ነውና። ሌባ አገር አስተዳዳሪ ነውና!!
“አስገራሚውና አነጋጋሪው ጉዳይ ህወሃት መቼ ነው ዘርፎ የሚጠግበው?” የሚለው ነው። አንድ ነጻ አውጪ ድርጅት አገር መምራቱ በራሱ ይገርማል፤ ምን አልባትም በዓለም ላይ በነጻ አውጪ የምትገዛ ብቸኛ አገር ኢትዮጵያ ትሆናለች ። በዚህም ላይ ይህ “ነጻ አውጪ” ከፍተኛ አመራሮቹ እንደሚሉት ከበረሃ ጀምሮ ዘርፎ ዘርፎ አለመጥገቡ ያስደንቃል። ከሁሉም በላይ የሚያስገርመው ግን በየቀኑ የጠላቶቹን ቁጥር በሺህዎች እያባዘ ነገ ምን ሊገጥመው እንደሚችል ያለመገመቱ ነው።
እዚህ ላይ አጠንክረን የምንለው ይኖረናል። ህወሃት አንዱን ከሌላው በማጋጨት መሰረት ላይ በተከለው ፖለቲካ የትግራይ ህዝብ የሌላውን ብሔረሰብ ህዝብ ሙሉ በሙሉ እንዲጠረጥርና ራሱን እንዲከላከል እየሰራ መሆኑን እናውቃለን። የማያውቁና መረጃ የሌላቸው ከግምት በላይ ይረዱታል። ይህ ሰይጣናዊ አካሄድ ዋጋው አስቀድመን እንዳልነው “ደም” ነውና ከወዲሁ ማርገቢያ እንዲበጅለት እናሳስባለን።
በቁጥር እየከፋፈሉ በምስጢር ከየአይነቱ በማስታጠቅ የትግራይ ህዝብን ከሌላው ህብረተሰብ ጋር ለማጋደል በምርጫ 97 ወቅት ሟቹ አቶ መለስ የሰጡትን ትዕዛዝ አጠንክሮ መያዝ አሁንም መዘዙ የከፋ ነውና ህዋሃት ከዚህ ተግባሩ እንዲታቀብ እንመክራለን። በወቅቱ “ራስህን ተከላከል፣ ሊያጠፉህ ነው” በሚል በመታጠቅ በየቀበሌው ለመተላለቅ መመሪያ የተጠበቀበት ደረጃ ተደርሶ እንደነበር ለምናውቅ ድርጊቱን ስናስበው ይቀፈናል። ያመናል። ያስበረግገናል። ተከስቶ ቢሆን ኖሮ ጠባሳው ምን ያህል በከፋ ነበር?
የትግራይ ህዝብ እንደ ህዝብ እንደ ማንኛውም የተረገጡ ዜጎች ሁሉ የስርዓት ለውጥ ያስፈልገዋልና ሌላው ህብረተሰብ ከጭፍን ጥላቻ ራሱን እንዲያርቅ እንመክራለን። የትግራይ ልሂቃንም በገለልተኛ ሚዛን በራሳቸው ላይ እንዲሆን የማይፈቅዱት በሌሎች ላይ እየተደረገ መሆኑንን በመቃወም በህዝብ መካከል የተረጨውን መርዝ በማምከን ተግባር ላይ ሊሰማሩ እንደሚገባ ለመጠቆም እንወዳለን። ዙሪያችንን የከበቡን ጠላቶች ይበቁናልና!!
ኢህአዴግ እንደ ገዢ ያለው አቅም ተቦርቡሯል። ሟርት ነው ካልተባለ የኑሮ ብሶት፣ ሌብነትና በሌላው ህዝብ ላይ የሚፈጽመው የግፍ ክምር ሊንደው ተቃርቧል። የሚመካበት የጦር ሃይልም ቢሆን ወገን አለውና አንድ ቦታ ከተፈረከሰ አደጋው የአገር ነው። በቡድን አደራጅቶ መሳሪያ በማደል በጎጥ ወኔ የህዝብን ቁጣና ምሬት መቋቋም የሚታሰብ አይደለምና ህወሃት በመፈክር አታሎ በጨረሳቸው ታጋዮች ደም ላይ የሚደንሰውን ከልክ ያለፈ የጥጋብ ጭፈራ ይግታው። በነጻ አውጪ ስም አገር እየመሩ ዝርፊያ ተራ የማፊያ ተግባር እንጂ አገር እምራለሁ ከሚል ወገን የሚጠበቅ አይደለምና ያደባባይ ዝርፊያ ይቁም!! ኢህአዴግ ሌባ ወይስ አገር አስተዳዳሪ በማለት የሚጠይቁ ሁሉ እውነት አላቸውና ልብ ያለው ልብ ይበል።
በግብር የምናየው ኢህአዴግ ከተዘፈቀበት ችግር ራሱን ከማጽዳት፣ ህዝብ የሚበጀውን እንዲመርጥ መንገድ ከማመቻቸትና አገሪቱን ወደ መልካም ጎዳና ከማሸጋገር ይልቅ፣ ህዝብን በጅምላ “ለሃጫም” እያለ መስደብ የሚያስደስተው ነው። ህዝብን “ጠባብ፣ አሸባሪ፣ ጸረ ልማት፣ …” በማለት መፈረጅ የድል ያህል የሚያስፈነድቀው ነው። ራሱ ስራ ፈት ያደረገውን ትውልድ “ቦዘኔ” ሲልና ሲሳደብ የስኬት ገድል ያስመዘገበ ያህል ይመስለዋል። ከሁሉም በላይ የህወሃት የእጅ ስራ ውጤት የሆኑ አሻንጉሊት ካድሬዎች እንደ ጌቶቻቸው “ለሃጫም” እያሉ ህዝብን ሲሰድቡ ሽልማት ለመስጠት ይሽቀዳደማል። ህዝብ ሲያኮርፍና ሲበሳጭ ይደሰታል። አገሪቱን ባህር አልባ አድርጎ ስለቀረቀረባት ኩራት ደረቱን ይነፋል። በማያገባው ጦርነት ምስኪን ወገኖችን ማሽጨፍጨፉ ልዩ ገድል ሆኖ ይታየዋል። ድንግል መሬት በሳንቲም ሲቸበቸበ ልማት ነው ይላል፡፡ ነዋሪዎችን ለትውልድ ከኖሩበት እያፈናቀለ መሬታቸውን ለውጪ ባለሃብቶች እየሰጠ “እስካሁን ያልሸጥነው መሬት ነው የሚያሳስበን” በማለት በሰው ደም ይቀልዳል፡፡ በዚህ ሁሉ ትዕቢቱ ላይ ንጹሃንን እያሰረ ማሰቃየቱ፣ መግረፉና መግደሉ፣ አሁን አሁን ይፋ የሆነበት የመርዝ ጣጣ ጀብድ ሆኖበታል። በልክ በልኩ የሰራቸውን አሻንጉሊት ተላላኪዎቹ ሰብስቦ በሚሰራው ድራማ መደነሱና ውሸታም አገር አስተዳዳሪ መሆኑ የኩራቱ ሁሉ ኩራቱ ነው። በዚህ ሁሉ ሲደመር ዜሮ በሚሆን ትምክህት ውስጥ ሆኖ አገር መምራቱ በእጅጉ ያሳስበናል፣ ያስጨንቀናል፣ ወደፊት የሚመጣውን ስናስበው እንደ ዜጋ ያስበረግገናል። ለዚህ ነው “ኢህአዴግ ሌባ – ወይስ አገር መሪ” ስንል የጠየቅነው። መልሱን የሚሰጥ ሁሉ እንዳመላለሱ ትግሉን ሊያካሂድ ይገባዋል እንላለን፡፡
http://www.goolgule.com/eprdf-thief-or-administrator/