Saturday, March 22, 2014

(ሰበር ዜና) ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ከሀገር እንዳይወጣ በኢሚግሬሽን ታገተ

ሰማያዊ ፓርቲ እንዳስታወቀው በአሜሪካን ሀገር ስቴት ዲፓርትመንት የተዘጋጀለትን ወጣት የአፍሪካ መሪ የሚል ሽልማት ለመውሰድ ዛሬ ሌሊት ወደ አሜሪካ ያቀና የነበረው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በቦሌ አየር መንገድ ከተገኘ በኋላ ከሀገር መውጣት አትችልም በሚል ታግቶ ይገኛል፡፡ በረራው 4 ሰአት ላይ የነበረ ሲሆን እስካሁን እስከሌሊቱ 8 ሰኣት ድረስ ታግቶ ይገኛል፡፡
ዝርዝር መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን።

No comments:

Post a Comment