Friday, August 30, 2013

ሰላማዊ ትግልን የሚገድብ ህገወጥ መመሪያ ተግባራዊ ሆነ


የአዲስ አበባ መስተዳድር ካቢኔ በተለይ የአንድነት ፓርቲን ህዝባዊ ንቅናቄ ለማፈን የሚያስችል አዲስ የሰላማዊ ሰልፍና የሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ መመሪያ በማዘጋጀት በህገወጥ መንገድ ተግባራዊ ማስደረጉ ታወቀ፡፡
ካቢኔው ያፀደቀው አዲሱ መመሪያ አንድነት ፓርቲ በመላ ሀገሪቱ እያደረገ ያለውን ስኬታማ ህዝባዊ ንቅናቄ ግምት ውስጥ የከተተ እንደሆነ ማንነታቸው እንዲገለፅባቸው ያልፈለጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ ኃላፊ ለአንድነት ፓርቲ አመራሮች ገልፀዋል፡፡ የፖሊስ ኮሚሽን ኃላፊው እንደሚሉት ነሃሴ 10 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ካቢኔ የፀደቀውና ለኮሚሽኑ የተላከው መመሪያ ከሕዝብ ፊርማ ለማሰባሰብ፣በራሪ ወረቀት ለመበተን፣ በማይክራፎን ለመቀስቀስና ፖስተር ለመለጠፍ ውስብስብና የተለያዩ አካላትን ፍቃድ ማግኘትን የግድ የሚል ነው፡፡ ሃላፊው “መመሪያው በተለይ የአንድነት ፓርቲ እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ውጤታማ እንይሆን በችኮላ ተግባራዊ የተደረገ ነው፡፡” በማለት ጨምረው አስረድተዋል፡፡
የመመሪያው አወጣጥ ህገወጥነት እንደተጠበቀ ሆኖ መመሪያው በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ሳይወጣና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትም ሳይሰራጭ፤ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ህገወጡን መመሪያ እንዲያስፈፅም ከአዲስ አበባ መስተዳድር ከንቲባ ጽ/ቤት ትእዛዝ መተላለፉ በኢትዮጵያ የህግ የበላይነት እንዳበቃለት የሚያሳይ ነው፡፡
የመመሪያው ህገወጥነት አሳሳቢ በመሆኑ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና የፓርቲው ዋና ፀሀፊ አቶ አስራት ጣሴ ከአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ግርማ ካሳና ከኮሚሽኑ 3 ከፍተኛ ሀላፊዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ህገወጡን መመሪያ ፖሊስ ኮሚሽኑ እንዲያስፈፅም መታዘዙን አረጋግጠዋል፡፡
“መመሪያው በ1983 ዓ.ም ከወጣው (አዋጅ ቁጥር 3/1983 ዓ.ም ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ሥርዓት የወጣ አዋጅ ገጽ 12) አዋጅ ጋር የሚጣረስ ነው፣ በአዋጁ የአዲስ አበባ መስተዳድር የራሱን መመሪያ ማውጣት እንደሚችልም የሚገልፅ ነጥብ የለም፡፡ ” በሚል የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የአዲስ አበባ መስተዳድር ከንቲባ ጽ/ቤት ሃላፊዎችን ቢጠይቁም የከንቲባ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው “ለሰኞ ተመካክረን ምላሽ እንደጣችኋለን” የሚል ምላሽ ሰጥተዋቸዋል፡፡
የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ከሰአት ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስለመመሪያው የሚያውቀው ነገር እንዳለ በቦርዱ ጽ/ቤት በአካል ተኝተው ጥያቄ ቢያቀርቡም የቦርዱ ዋና ፀሀፊ አቶ ነጋ “ምርጫ ቦርድ እንዲህ አይነት መመሪያ ስለመውጣቱ የሚያውቀው ነገር የለም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
አንድነት ፓርቲ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል በመላው ሀገሪቱ እያካሄደ ላለው ህዝባዊ ንቅናቄ ከህዝብ ፊርማ ሲያሰባስቡ፣በራሪ ወረቀት ሲበትኑና የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያካሂዱ ከ72 በላይ የሚሆኑ አባላቱ በአዲስ አበባ ህገወጥ እስር ተፈፅሞባቸው እንደነበር ይታወሳል፡፡

Nebyu Hailu

ሰበር ዜና የአገር ውስጥ የደህንነት መምሪያ ሃላፊው አቶ ወልደሥላሴ ወልደሚካኤል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ፤

     August 30, 2013        
esat
የአገር ውስጥ የደህንነት መምሪያ ሃላፊው አቶ ወልደሥላሴ ወልደሚካኤል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ፤
ፋና እንደዘገበው ፤ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋሉት የነበራቸውን ስልጣን ያለአባብ በመጠቀም ምንጩ ያልታወቀ ሃብት በማፍራት የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው ነው ።

ፋና ይህም ቢልም አቶ ወልደስላሴ -ከደህንነት ዋና ሹሙ ከአቶ ጌታቸው አሰፋ ጋር ጠብ ውስጥ ገብተው መቆየታቸው በስፋት ሲነገር ቆይቷል።
በተለይ መቀሌ በተካሄደው የህወሀት ጉባኤ ላይ በአቶ ጌታቸው አሰፋ እና በአቶ ወልደስላሴ መካከል ከፍተኛ ጭቅጭቅ ተፈጥሮ የነበረ ሲሆን፤በጉባኤው አቶ ወልደስላሴ-አቶ ጌታቸው አሰፋን “የአል አሙዲ ተላላኪ ሆኗል” እስከማለት ድረስ ዘልፈዋቸው ነበር።
በዚህም ሳቢያ የደህንነት ሹሙ አቶ ጌታቸው ቂም በመያዝና ከወራት በፊት በተደረገ ግምገማ አቶ ጌታቸውን ከሙስና ጋር በማያያዝ ከሀላፊነታቸው እንዲወገዱ አስደርገዋቸዋል።
ከወራት በፊት በዚህ መልኩ ከሀላፊነታቸው የተወገዱት አቶ ወልደሥላሴ ዛሬ በሙስና ክስ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከፌደራል ስነምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው ፥ ተጠርጣሪው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ቀርበው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል።
የዛሬ አመት ገደማ ኮሚሽኑ በአቶ ወልደስላሴ ወንበር ላይ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩትን አቶ አይቼው ተፈታን በተመሳሳይ ወንጀል ከሷቸው በአሁን ጊዜ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንደሆነም ፋና ጨምሮ ዘግቧል ።
አቶ ወልደስላሴ የህወሀት አባልና የትግራይ ልማት ማህበር የቦርድ አባል ናቸው።
ጸረ-ሙስና ኮሚሽን የውስጥ ተቀናቃኞችንና አፈንጋጮችን ማጥቂያ እንደሆነ ይታመናል።

Thursday, August 29, 2013

የእኛ “መንግስት” (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)

የእኛ “መንግስት” (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)
107521ee73facb2e1377756991
August 29, 2013
“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም” ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡Journalist Temasegan Dasaleg

እናም የስርዓቱን የአስተዳደር ዘይቤ ያለፍርሃት አደባባይ ካዋልነው የቀድሞ ገዥዎቻችን የተጓዙበትን ጎዳና እየተከተለ መሆኑን ለመተንተን የምሁራንን ጥናት መጠበቅ ግድ አይለም፤ ምክንያቱም ለዓመታት የተመለከትነው እውነታ የሚነግረን የአመራሩን እና በዙሪያው የሠፈሩ የጥቅም ተጋሪ ግለሰቦችን ብልፅግና ታሳቢ ያደረገ፣ ከታግሎ መጣል ህግ የተቀዳ፣ የራስ ሀገርንና የራስ ሕዝብን በምርኮ ያስገበረ ፖለቲካ መንበሩን ነው፤ ገብር፣ ገብር፣ ገብር…!!
ዛሬ መንገድ ዳር ረሀብ አዙሮ የጣለው ወንድምህ ስቃይ እንደ ጥላ የሚከተልህ፤ ህፃናት በትምህርት ገበታቸው ላይ በጠኔ ተሸንፈው መመልከቱ የሰርክ አሳዛኝ ክስተት የሆነብህ ከሰው ሰራሽ ችጋር፣ ከሰው ሰራሽ የቀዬ ፍንቀላ፣ ከሰው ሰራሽ እርዛት… የመነጨ መርገምት እንጂ የሰማይ ቁጣ አይምሰልህ፤ እመነኝ መለስም ሆነ ተተኪዎቹ ስኬት አድርገው የሚሰብኩትም ይህንን ነው፤ ‹ሀገር አቀናን!› የሚሉትም ይህንን ነው፤ ሰሞኑን የሚያሰለቹህ ተረኛ ምሁራንም ‹‹ትምህርትና ጤናን በተመለከተ መለስ ‹እልል› የሚያስብል ሥራ ሰርቷል›› የሚሉህ ጣራና ግድግዳ እየቆጠሩ ነው፤ ይህ አይነቱ መደዴ ሙገሳም ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ሪፖርት ለማዘጋጀት ከሚረዳ ቁጥር የዘለለ አበርክቶ አንደማይኖረው አትዘንጋ፡፡
እውነት እውነት እልሀለሁ፡- ይህ የሆነበት ብቸኛው ምክንያት መንግስት በስልጣን ላይ ስለሚቆይበትመንገድ ብቻ መጨነቅን ግዴታው በማድረጉ ነው፤ ይህንን ለመረዳትም እያገባደድን ባለው ክረምት የመንግስት ትኩረት በምን ላይ አንደሆነ የሚያሳይ ማስረጃን ጨርፌ ላሳይህ፡፡
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የእስልምና እምነት ተከታዮች መንግስት በሃይማኖታቸው ጣልቃ መግባቱን በመቃወም እና የታሰሩ ኮሚቴዎቻቸው እንዲፈቱ በመጠየቅ እያደረጉ ያለውን ትግል በሰላማዊ መንገድ አጠንክረው ሲቀጥሉ፤በተቃራኒው ‹‹ፀጥታ አስከባሪዎች›› አንዳንዴ በጥይት፣ አንዳንዴ በአስለቃሽ ጢስ፣ አንዳንዴ በማጋዝ…ምላሽ ሲሰጡ…
በርግጥ መንግስት ከኃይል እርምጃው በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎችን (በምን አግባብቶ ወይም በምን አስፈራርቶ እንደሆነ ባይታወቅም) ወደ አደባባይ በማስወጣት መብት ጠያቂዎቹን ከ‹‹አክራሪ››ነት እና ‹‹ወሃቢዝም››ነት ጋር አያይዘው የውግዘት በረዶ እንዲያዘንቡባቸው እያደረገ ነው፡፡ ኢቲቪም ይህንን ኩነት እየተከታተለ ማራገቡን ቀጥሎበታል፤ ‹‹የቲፒ ከተማ ነዋሪዎች ‹አክራሪዎችን አወገዙ››፤ ‹‹በደቡብ ወሎ ኩታ በር ዞን አንድነት ፓርቲ ህገ-ወጥ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰልፍ ተካሄደ››፤ ‹‹የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ‹የሼሁ ግድያ ድራማ አይደለም› አሉ፣ ‹የሼህ ኑሩ ኢልም ነው፣ የአሸባሪዎች ብር ነውም›ብለዋል››፤‹‹የመርሀቤቴ ነዋሪዎች ፅንፈኞችን በመቃወም የአቋም መግለጫ አወጡ››፤…
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- አንድነት ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የ‹‹ፀረ-ሽብር ሕጉ›› እንዲሰረዝና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ እና የአዳራሽ ስብሰባዎችን እያካሄደ ነው፤ መንግስትም አንዳንዴ የአፀፋ የድጋፍ ሰልፍ ሲያካሄድ፤አንዳንዴ የአዳራሽ ስብሰባዎች ከመካሄዳቸው አስቀድሞ ‹መጋኛ› ሲሆንባቸው፤ አንዳንዴም የአስተባባሪዎቹን መኪና ጎማ ሲያፈነዳ፤ አንዳንዴም አዳራሽ ከልክሎ ሲያደናቅፋቸው… መዋሉ ፋታ የነሳው ይመስላል፤ በወላይታ የተጠራውን የአዳራሽ ስብሰባም ‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ የትውልድ ቦታ እንዴት ተደርጎ!›› ያሉ ካድሬዎች የአንድነት ሰዎችን አዋክበው ስብሰባውን አክሽፈዋል፤
ክረምቱእንዲህእየተገባደደነው፡-ገዥው ፓርቲ ‹የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ አንደኛ ሙት ዓመት አከብራለሁ› በሚል መላ ኢትዮጵያን ችግኝ መትከያ፣ መላ ዜጎቿን ደግሞ ወደ አርሶ አደርነት በአስማት የቀየራቸው አስመስሏቸዋል፤ቴሊቪዥንና ራዲዮንም አስፈላጊነታቸው በየመንደሩ ችግኝ መተከሉን እየተከታተሉ መዘገብ ብቻ እስኪመስል ድረስ እንዲህ ሲሉ ጀምበር ወጥታ ትጠልቃለች፡- ‹‹የላይ አርማጮህ ነዋሪዎች ችግኝ ተከሉ››፣ ‹‹በመቀሌ ከተማ ‹ዘመቻ መለስ› በሚል የችግኝ ተከላ ተካሄደ››፣ ‹‹አቃቂ ኮረብታ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ችግኝ በኦሮሚያ ፌደራል ፖሊስ አባላት ተተከለ፤ ቦታውም ‹መለስዜናዊ ኮረብታ› ተብሎ ተሰይሟል››፣ ‹‹በምዕራብ ሀረርጌ አስራ ሰባት ሚሊዮን፣ በወልበራ አስራ አራት ሚሊዮን ችግኝተ ተክሏል››፣ ‹‹በመንዝ ላሎ ወረዳ ተቆጥሮ የማያልቅ ችግኝ ተከላ ተደርጓል››፣ ‹‹የብአዴን አመራርና ካድሬ በባህር ዳር ከተማ በቢሊዮን የሚቆጠር ችግኝ ተከሉ፤ በፕሮግራሙ ላይ ጓድ አዲሱ ለገሰ ‹ችግኝ የምንተክለው አገሪቱ በአረንጓዴው ልማት በአለማችን ማግኘት የሚገባትን ቦታ እንድታገኝ ለማድረግ ነው› ሲል፣ ጓድ በረከት ስምዖን ደግሞ ‹ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአለማችን በአንድ ጊዜ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ችግኝ እየተከሉ ያሉባት ብቸኛ ሀገር ናት› ብሏል››፤‹‹ዝክረ መለስ 1ኛ ዓመት መታሰቢያን ምክንያት በማድረግ ከሐምሌ አስራ አምስት ቀን ጀምሮ ሁሉም ቀበሌዎች በስሙ ‹ፓርክ› ሰይመው ችግኝ ተከላ እያካሄዱ›› መሆኑን ደግሞ የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ መግለፁን የአማራ ክልል ብዙሃን መገናኛ ዘግቧል፤ ‹‹በወልቂጤ ከተማ በተደረገው ችግኝ ተከላ ላይም አንዲት ወጣት ‹መለስ ለሴቶች የተለየ አመለካከት ነበረው›› ማለቷም በዘገባው ተጠቅሷል፤ …ማን ነበር የመለስ ራዕይ ‹ችግኝ መትከል ነው› ያለው? …ኢህአዴግ ይሆን?
ከዚሁ ጎን ለጎን (አሁንም ሙት ዓመቱን ለማሰብ) በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የእግር ጉዞ ተደርጓል፣ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓትም ተካሄዷል፤መነሻውን መቀሌ፣ መድረሻውን አዲስ አበባ ያደረገ ‹‹የመለስ ቱር አረንጓዴ ልማት›› የብስክሌት ውድድርም ሊጠናቀቅ ገና አንድ ሳምንት ይቀረዋል፤ በብሄራዊና ሀይማኖታዊ በዓላት ቀንለሃያ አንድ ጊዜ ይሰማ የነበረው የመድፍ ድምፅም፣ የመለስን አንደኛ ሙት ዓመት ለማብሰር ተተኩሷል፤ …በግድ አልቅሱ፣ በግድ ተዝካር አውጡ፣ በግድ ችግኝ ትከሉ፣ በግድ ተወያዩ፣ በግድ አደባባይ ውጡ፣ በግድ የፎቶ ግራፍ ኤግዚቢሽን ጎብኙ፣ በግድ.. ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ሽፈራው ሽጉጤ ከአንድ ሺህ ሰባት መቶ በላይ ለሚሆኑ የዩኒቨርስቲ ከፍተኛ መምህራን ‹የአቅም ግንባታ ስልጠና› እየሰጡ ነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምሁራኖቹን ማሰልጠን ያስፈለገበት ምክንያት ‹‹ብቃት ያለው ምርጥ የተማረ ኃይል ለማፍራት››መሆኑን ቢነግርህ አይግረምህ፤ ይህ ኢትዮጵያ ነውና የዐዋቂነት ማረጋገጫው መማር፣ ማንበብ፣ መመራመር… አይደለም፣ የፖለቲካውን ኃይል መያዝ እንጂ፤ ‹ስልጣን ላለው ሁሉምሚስጥረ-ጥበብይገለፅለታል› እንዲል አብዮታዊ ዲሞክራሲ መለስ ዜናዊም በሁሉም መስክ ‹አስተማሪ› ነበር፤ የህግ ባለሙያዎችን ሰብስቦ የሀገሪቱን ወንጀለኛ መቅጫ ህግ ትርጓሜ ሲተነትን ደጋግመህ ሰምተኸዋል፤ በቀጣዩ ቀን ደግሞ ለግብርና ባለሙያዎች ከውሃ ማቆር እስከ በላብራቶሪ የሚዳቀል ምርጥ ዘር ድረስ ባሉጉዳዮችዙሪያ የሁለት ቀን ማብራሪያ መስጠቱን ታስታውሳለህ፤ እመነኝ ተተኪው ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ ነው እያደረገ ያለው፤ የሆነ ሆኖ ኃ/ማርያም ለምሁራኖች ከሙያቸው ጋር ስለተያያዙ ጉዳዮች ጭምር በሰጣቸው ስልጠና ላይ እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀርቦለት ነበር ‹‹የኢንዱስትሪዎች በበቂ ሁኔታ አለመኖሩ፣ በክፍል ውስጥ የምናስተምረውን ንድፈ ሃሳብ በተግባር ለማሳየት እንቅፋት ሆኖብናል››፤ በርግጥጠቅላይ ሚንስትሩ‹‹መፍትሄ››ያለውን የተናገረው ብዙም ሳይጨነቅ ‹‹እኔ ኢንዱስትሪን ‹ዲፋይን› የማደርገው ግብርናም ኢንዱስትሪ ነው ብዬ ነው››በማለት ነበር፤…ግና!ይህ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በተጨባጭ አላብራራም፡፡ለምሳሌ ህክምና የሚያጠና ተማሪ በምን መልኩ በሞፈርና ቀንበር የተግባር ልምምድ ማድረግ እንደሚችል፤ወይም ፖለቲካ ሳይንስ የሚያጠና ተማሪ የተግባር ልምምዱን በግብርና ኢንዱስትሪ እንዴት ሊወጣው እንደሚችል? ማለቴ ነው፡፡
ለዓመታት በርካታ ምሁራን ብቃት አልባ ተማሪዎች እንደ ሰማይ ከዋክብት የመብዛታቸው መንስኤን ከትምህርት ፖለሲው ጋር የሚያነፃፅሩበትን ሀቲት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ ባገኘው የሀገር መሪነት ስልጣን ገልብጦ በዩንቨርስቲ ቆይታው መምህራኖቹ የነበሩትንም ጭምር ‹‹አቅም አንሷችኋልና-እገነባችኋለሁ›› ሲል ከመስማት የከፋ እንደ ሀገር ክሽፈት የለም (በነገራችን ላይ ከወራት በፊት ለኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በረከት ስምዖን፣ ቴውድሮስ አዳህኖም፣ ሶፍያን አህመድ በአጠቃላይ ሁሉም የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አንድ ህንዳዊ ፕሮፌሰር በኢህአዴግ ጽ/ቤት ‹‹ልማታዊ መንግስት›› እንዴት ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል ሲተነትንላቸው፣ እነርሱም ደብተርና እስክርቢቶ ይዘው በንቃት ሲከታተሉ የቴሌቪዥ ዋና ዜና ሆኖ የቀረበበትን ምክንያት ዛሬም ድረስ ሊገለፅልኝ አልቻለም፤ በተለይም ፕሮፈሰር እንድርያስ እሸቴ ‹‹በቃሉ የፀና…›› በሚል ርዕስ መለስን አስመልክቶ በተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም ላይ ‹‹በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ ልማታዊ ስርዓተ መንግስት ‹ዴሞክራሲያዊ ሊሆን ይችላል፤ መሆንም አለበት› ብሎ በአደባባይ የተከራከረው እኔ እስከማውቀው ድረስ መለስ ነበር›› ማለቱን፣ ተተኪዎቹ ፍልስፍናውን ገና እየተማሩት ከመሆኑ አንፃር ስናየውሀገራችን ያለችበት ሁኔታ ጉዞው ወዴት ነው? ያስብላል፡፡ …ከቶስ በተማሪ ፖለቲከኛ የሚተዳደር ሕዝብ ከኢትዮጵያ በቀር ወዴት ይኖራል?)
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የህዳሴውን ግድብ ከዳር ለማድረስ በቂ ገንዘብ ስላልተገኘ ተደጋጋሚ የቦንድ ሽያጭ እየተካሄደ ነው፤ አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞችም በካድሬ ባልደረቦቻቸው ጫና በድጋሚ ቦንድ ለመግዛት መወሰናቸው ተሰምቷል፤ በርግጥ ከፍተኛ የኢህአዴግ የአመራር አባላት በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ቦንድ እንዲገዙ ለመቀስቀስ የአዘጋጇቸው ስብሰባዎች ‹‹ቅድሚያ የዜጎች መብት ይከበር›› ባሉ የሀገራችን ልጆች መክሸፉም የክረምቱ የመንግስት ዋና ሥራ ነው፤ ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- በነቢብ የኢትዮጵያ፣ በገቢር የገዥው ፓርቲ የግል ንብረት የሆነው ቴሌቪዥን ጣቢያ ባለፉት ሶስት ወር ብቻ ከሃያ በላይ ‹‹ዶክመንተሪ ፊልም›› አሳይቷል (ገና ይቀጥላልም) በርዕሳቸው እንደሚከተለው እንዘርዝራቸው፡- ‹‹ኢፍቲን›› በሶማሊያ ላይ የሚያጠነጥን፣ ‹‹የጥቁር ህዝቦች ልሳን (መለስ በአፍሪካ)››፣ ‹‹ከፓን አፍሪካ እስከ አፍሪካ ህዳሴ›› የጠቅላይ ሚንስትር መለስን ህይወት የሚዳስስ፣ ‹‹ዘመነ አፍሪካ››፣ ‹‹የአፍሪካ ልሳን-መለስ››፣ ‹‹መለስ ማን ነው?››፣ ‹‹ሀገሬ-ቤቴ››፣ ‹‹ባለራዕዮቹ›› ስራ ፈጠራ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ደውል›› እና ‹‹ደውል 2›› ህገወጥ-የሰዎች ዝውውርን በተመለከተ (በተለያያ ጊዜ የተላለፉ)፣ ‹‹የዲያስፖራ የልማት እንቅስቃሴ››፣ የካርታ ስራ ድርጅትን በተመለከተ፣ ‹‹የጥልቅ አስተሳሰብ ባለቤት›› በፕ/ር እንድርያስ እሸቴ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥን፣ ምድር ባቡር ኮርፕሬሽንን በተመለከተ፣ ‹‹ያልተለመደ ጉብኝት›› የአዲስ አበባ አስተዳደር የአምስት ዓመት የመንግስት ግንባታዎችን በተመለከተ፣ ‹‹ሼህ ኑር ለምን ሞቱ?›› የደሴውን ሼህ ኑር ይማምን ግድያ በተመለከተ፣ ‹‹የተስፋ ስንቅ››፣‹‹በቃሉ የፀና›› በድህረ መለስ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ያልተጠኑ ገፆች›› በመለስ ዜናዊ ህይወት ዙሪያ (በርግጥ በዚህ ፊልም እህቱ ጠላ፣ ወንድሙ አንባሻ በመሸጥ መተዳደራቸውን በምስልም በድምፅም ማቅረቡ ምን የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ እንደሆነ ለማወቅ ግራ ያጋባል፤ …ምናልባት እንዲያ እየዘረፈ ለቤተሰቦቹ ‹ሶልዲን› የማይሰጥ ‹ቆነቋና› ነበር ለማለት ይሆን? ወይስ ለአዜብ መስፍን ‹የወር ቀለባችንን እንቸገራለን› የአንድ ሰሞን ማስተዛዘኛ ምስክር ፍለጋ ነው?
በጥቅሉ ለኢህአዴግ ሕዝብን የማስተዳደር፣ ሀገርን የመምራት መገለጫ ይህ ነው፤ ሌላ አይደለም፤ ግና! ለዘመናት ያልተመለሱ ጥያቄዎቻችን ዛሬም መጮኻቸውን አላቋረጡምና እነሆ እንዲህ ቀጥለዋል፡- ሀገር ማስተዳደር ‹መለስ ጀግና ነበር› እያሉ ማሰልቸት ነውን? የመንግስትስ ስራ (ግዴታ) ምንድር ነው? ሀገሪቱን ‹‹መለስ-ፓርክ›› ወደሚል ስያሜ ከመቀየራችሁ በፊት፣ ለጤፍ ዋጋ አለቅጥ መናር ምክንያቱን ስለምን መመርመር ተሳናቸው? ሀገሪቱን በ‹አራጣ› እንደያዘ ስግብግብ ነጋዴ በሚሊዮኖች ህይወት ላይ የማይሞላ ‹ሳፋ› ደቅኖ አዋጣ፣ ግዛ፣ ክፈል፣ ገብር… እያለ የሚያስጨንቀው ማን ነው? ስለመለስ ‹የሃሳብ ምጡቅነት› መስካሪ ምሁራኖቻችን ለጎዳና ኑሮ የተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ስንት ሚሊዮን እንደደረሱ እና እልፍ አላፍት ታዳጊዎቻችን በሴተኛ አዳሪነት እንደተሰማሩ የምትነግሩን መቼ ነው?እንዲህ የመሆኑ ምክንያትስ በማን ይሆን? ‹የሁለት ዲጂቱ›ዕድገት ሸክምን የማለዘብ አቅም ከሌለውፋይዳው ምንድር ነው? ‹ሳቅ ትዝታ› ስለሆነባቸው ጎጆዎች ለምን አትነግሩንም? መለስ ‹ያለመለማት› ኢትዮጵያ ወዴት ትሆን? ‹ፖለቲካ› ማለትስ ይህ ነውን? …ነጋ ድራስ ገ/ህይወት እንዳሉት ‹‹…መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡›› የመተራረሚያው ጊዜም በጣም ያለፈ ይመስለኛል፡፡ አገዛዙን ‹እንደ መንግስት› መቀበሉም እንዲሁ፡፡

የአዲስ አበባ መስተዳድር ሰማያዊ ፓርቲ በመጪው እሁድ ሰልፍ የሚያደርግ ከሆነ፤ሰልፉ ህገወጥ ነው አለ።



ኢሳት ዜና :- ሰንደቅ እንደዘገበው በመጪው እሁድ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በማወዛገብ ላይ ነው።
ቀደም ሲል ሰማያዊ ፓርቲ በዕለቱ ሰልፍ እንደሚያካሂድ ቢያስታውቅም፤ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት በበኩሉ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው መግለጫ በተመሳሳይ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን ይፋ አድርጓል።
ይህንን ተከትሎ በፓርቲው እና የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ “የቀደምኩት እኔ ነኝ” በማለት በመወዛገብ ላይ ሲሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና የስብሰባ ማሳወቂያ ጽ/ቤት በበኩሉ፤ ሰልፍ እንደሚካሄድ ቀድመው ያሳወቁት የሃይማኖት ተቋማቱ በመሆኑ በዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ የሚካሄድ ከሆነ ህገወጥ ነው ብሏል።
ስለጉዳዩ ተጠየቁት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ፤ ፓርቲው ከወር በፊት ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሂድ በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ ማድረጉን በማስታወስ፤ ፓርቲያቸው ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ በቅድሚያ ጥያቄ ማቅረቡን ተናግረዋል።
እንደ ሊቀመንበሩ ገለፃ ፓርቲው አስቀድሞ ቀን መቁረጡንና በተባለውም ቀን ሰልፉን ለማካሄድ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍ፣ ስብሰባና የማኀበራት ፈቃድ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ ጭምር የማሳወቂያ ደብዳቤ ማስገባቱን ተናግረዋል።
በወቅቱ ጽ/ቤቱ ደብዳቤውን ለመቀበል ፍላጎት ባያሳይም በህጉ መሠረት ማሳወቅ ብቻ በቂ በመሆኑ ደብዳቤውን በጽ/ቤቱ አስቀምጠው መመለሳቸውንና በኋላም ጽ/ቤቱ በፖስታ ቤት በኩል በሬኮማንዴ ለፓርቲው ሰልፍ የት እንደሚያካሂድ፣ ምን ያህል ሰው እንደሚሳተፍ ማብራሪያ በመጠየቁ ፓርቲው በበኩሉ ለጽ/ቤቱ ወዲያውኑ ምላሽ መስጠቱን ተናግረዋል።
ሆኖም ጽ/ቤቱ በህጉ መሠረት በ48 ሰዓታት ውስጥ ምላሽ መስጠት ሲገባው ዝምታን በመምረጡ፣ ዝምታው ደግሞ ሰልፉ እንደተፈቀደ የሚጠቁም በመሆኑ በሰልፉ ዙሪያ ፓርቲው ዝግጅት ማድረግ መቀጠሉን አስታውቀዋል።
ከጽ/ቤቱ እስካሁን ደረስ ምላሽ ባለመገኘቱም ፓርቲው በዕለቱ የጠራውን ሰለማዊ ሰልፍ ከማካሄድ ወደኋላ የሚመልሰው የህግ መሠረት ባለመኖሩ ሰልፉን እንደሚያካሂድ አስታውቀዋል።
ፓርቲው ከነገ ሐሙስ ጀምሮ በአምስት ተሽከርካሪዎች በአስሩም ክፍለ ከተማ መጠነ ሰፊ ቅስቀሳ ለማካሄድ መዘጋጀቱን የተናገሩት ሊቀመንበሩ፤ በመላ ከተማዋና በአካባቢዋም በመቶ ሺህ የሚቆጠር ወረቀት እንደሚበተንና ሰልፉም ካለፈው ሰልፍ ልምድ በማግኘት ከፍተኛ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ባለፈው ሰኞ ነሐሴ 20 ቀን 2005 በዋና ጽ/ቤቱ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን ያስታወቀው የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የቦርድ ሰብሳቢ ርዕሰ ደብር በሪሁን አርአያ ፤ በዕለቱ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን እንደማያውቁና ጽ/ቤታቸውም ቀደም ብሎ ለሰልፉ ሲዘጋጅ መቆየቱን ተናግረዋል።
ርዕሰ ደብር በሪሁን አርአያ የሃይማኖት ጽ/ቤቱ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ያሳወቀበትን ቀን ለመናገር አልፈለጉም።
ከዚህም በላይ ሰንደቅ እንዳለው፤ የርዕሰ ደብር በሪሁን መግለጫ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት ሰልፉን ለማካሄድ ጥያቄ ያቀረበው ከነሐሴ 15 እና 16 በኋላ መሆኑን የሚያመለክት ነው። በአንፃሩ ሰማያዊ ፓርቲ የማሳወቂያ ደብዳቤ፡ያስገባው ግን ነሐሴ 16 ቀን 2005 ዓ/ም ነው።
ሀቁ ይህ ቢሆንም፤የአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማርቆስ ብዙነህ፦” የእውቅና ጥያቄ በማቅረብ ቀዳሚ የነበሩት የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት በመሆናቸው ሰማያዊ ፓርቲ በዕለቱ ሰልፍ እንዲያካሂድ አልተፈቀደለትም” ብለዋል።
አክለውም፦”ፓርቲው ሰልፍ የሚያካሄድ ከሆነም ህገወጥ ነው” ብለዋል።
ሁለቱም ወገኖች የሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ስላሳወቁበትን ቀን እና ስለ ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች ግን ከመናገር ተቆጥበዋል።

የሕወሐት ባለስልጣናት የአሜሪካ ቆይታ፤ የከዱ አሉ

August 29, 2013
ከኢየሩሳሌም አርአያ
በአባይ ወልዱ የሚመራውና ሰባት ከፍተኛ የሕወሐት ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን በአሜሪካ አራት ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ እንደገጠመው በስፍራው የተገኙ ምንጮች አስታወቁ። ቡድኑ በዋሽንግተን ኢትዮጲያ ኤምባሲ በጀመረውና በመቀጠል በላስቬጋስ፣ ሲያትልና ካሊፎርኒያ ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ “አላማ” አድርጎ የያዛቸው ጉዳዮች እንደነበሩ የጠቆሙት ምንጮች፣ እነሱም፥ “የመለስ ፋውንዴሽን፣ የአባይ ግድብና የ40/60 የቤቶች ግንባታ.” ሲሆኑ፣ ለነዚህ ማስፈፀሚያ “ገንዘብ አዋጡ” የሚለው ዋናው ግብ እንደነበር አስረድተዋል። በተለይ ደግሞ « በትግራይ ተወላጁ ዘንድ ሕወሐት የለም፣ ተከፋፍሏል፣ ተዳክሟል፣ ፓርቲው ሰው የለውም፤» የሚለውን እራሱ ቡድኑ በማንሳት ለገዛ ጥያቄው መልስ ሲሰጥ « ሕወሐት አሁንም ሃይል አለው፤ አልተዳከመም» በማለት አድራጊ- ፈጣሪ በመሆን ስልጣኑን በበላይነት ተቆጣጥሮ እንደያዘና ቡድኑ የመጣውም “አይዟችሁ” ለማለት እንደሆነ መገለፁን በቅርብ የተከታተሉት ምንጮች አስታውቀዋል። ቡድኑ በተጨማሪም ፥ « ልማት አልምተናል፤ ትግራይ እየለማ ነው፤ ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረገነው ነው» ከማለቱ ባሻገር « በትግራይ ተወላጁ ላይ አደጋ ተደቅኗል፤ የሙስሊሙ፣ የትምክህተኞችና የሽብርተኞች አደገኛ እንቅስቃሴ እያንዣበበ መሆኑን፣…የተደቀነብህን አደጋ ከጎናችን ሆነህ ተከላከል፤ ያለበለዚያ ግን ሊያጠፉህ ነው፤» ሲሉ መናገራቸውን የገለፁት ምንጮች አክለውም፣ « አባላት የሆናችሁ ተወደደም ተጠላ መሬትና መኖሪያ ቤት እንሰጣችኋለን፤ ለዚህም ከእኛ ጎን መሰለፍ አለባችሁ» በማለት ሊሸነግሉ መሞከራቸውን ጠቁመዋል።
ከዋሽንግተን ስብሰባ (ለሁለት ተከፍሎ ነው የተካሄደው) በኋላ ወደ ሶስቱ ከተሞች ተከፋፍለው እንደሄዱ ሲታወቅ፥ ሲያትል አቶ ብርሃነ ማረት፣ እንዲሁም ላስቬስጋስ አባይ ወልዱና ተክለወይኒ አሰፋ መሄዳቸው ታውቋል። በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ የገጠማቸው እነአባይ ስብሰባው ከቀኑ 2፡00 ሰዓት ይጀመራል ተብሎ ከአራት ሰዓት በኋላ ዘግይቶ አመሻሽ ላይ መጀመሩን ምንጮች ገልፀዋል። ስብሰባው ሲጀመር ከላይ የተገለፁትን ጉዳዮች ያደመጠው ተሰብሳቢ ተከታዮቹን ጥያቄ አቀረበ፤ « ዴሞክራሲ አለ ትላላችሁ፣ ነገር ግን ዴሞክራሲ የለም፤ በሃሳብ የሚቃወማችሁን ታስራላችሁ፣ ታንገላታላችሁ፣ የሰብአዊ መብት ረገጣ ታካሂዳላችሁ፤ ከእናንተ የተለየ ሃሳብ ያለውን ትፈራላችሁ፤ ለምንድነው ይህን ሁሉ የምታደርጉት?….በማ.ረ.ት.(ማህበር ረድኤት ትግራይ) በትግራይ ሕዝብ ስም የምትሰበስቡትን ገንዘብ ለአራጣ ብድር እና ለፖለቲካ መጠቀሚያ በመሳሪያነት እያዋላችሁት ነው። ለምን?….ትእምት (ኤፈርት) ማነው ባለቤቱ?..በማን ነው የሚመራው?..ማነው የሚቆጣጠረው?..ለመሆኑ ኦዲት ተደርጎ ያውቃል ወይ?..እነማናቸው እየተጠቀሙበት ያለው?» የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ጥያቄዎች እንደነበሩ ምንጮቹ የጠቆሙ ሲሆን፣ አባይ ወልዱ « እኔ አልመልስም፣ ተ/ወይኒ መልስ ይስጥበት» ቢሉም ነገር ግን ግልፅና አግባብ ያለው ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ወደ ማመናጨቅና ቁጣ ያመሩት ተ/ወይኒ በዚህ ድርጊታቸው በርካታ ተሰብሳቢዎችን እንዳሳዘኑ አስረድተዋል። በዚህ የተበሳጨው ተሰብሳቢ « ጥያቄያችን አልተመለሰም» በማለቱና ሁከትና ያለመደማመጥ በማየሉ ስብሰባው እንዲቋረጥ መደረጉን የጠቆሙት ምንጮች፣ የጥያቄና ተቃውሞው መብዛት ያስደነገጣቸው ባለስልጣናቱ የመረጡት ማምለጫ በላስቬጋስ ተወካያቸው በሆነውና መድረክ ሲመራ በነበረው አቶ ተወልደ በኩል፥ « አዳራሹን የተከራየንበት ሰአት አብቅቷል፤ ስለዚህም ስብሰባው አብቅቷል » በማለት በአስቂኝ ሰበብ መቋረጡን አያይዘው ገልፀዋል። እነአባይ ከአዳራሹ ሲወጡ ቀድሞ ውጭ ሆኖ ይጠብቃቸው በነበረው ተሰብሳቢ ውግዘትና ስድብ እንደደረሰባቸው ያስታወቁት ምንጮች « ሌባ..ሌባ…ሙሰኞች..» የሚሉ ተቃውሞዎች ጎላ ብለው እንደተሰሙ አመልክተዋል።
ስብሰባዎቹን የታዘቡ ወገኖች በሰጡት አስተያየት እንዲህ ብለዋል፤ « በአንድ በኩል ልማት እያካሄድን ነው፤ እያሉና ገንዘብ እየጠየቁ በሌላ በኩል “ትግራዋይ አደጋ ተደቅኖብሃል፣ ከጎናችን ሆነህ ተከላከል፤” ማለት እርስ በርሱ የሚጋጭና ድጋፍ የማግኛ የፖለቲካ የፖለቲካ ቁማር ነው። ያልተጠየቁትን የፓርቲውን ህልውና (ስለ ሕወሐት) አንስቶ መነገሩም አስገራሚና አጠያያቂ ነው።» ሲሉ ትዝብታቸውን የጀመሩት እነዚህ ወገኖች በማያያዝም፥ « እነዚህ ሰባት ባለስልጣናት ወደ አሜሪካ የመጡት ከነዘመዶቻቸው፣ ጋሻ ጃግሬዎቻቸው ሲሆን፣ ባለስልጣናቱ የመንግስት ወኪሎች እንደመሆናቸው – በማን ገንዝብ ነው የሚንቀሳቀሱት?..የሚለው መጠየቅ አለበት። በሕዝብ ገንዝብ እየተንፈላሰሱ እንደሆነ ግልፅ ነው። የትግራይ ተወላጁን ብቻ ለይተው ስብሰባ የሚጠሩት ለምንድነው?…በእርግጥ ስላሰቡለት ነው?…የሚሉት ሲፈተሹ .መልሱ በጭራሽ አይደለም ነው። አላማቸውና ትኩረት የሰጡት የትግራይ ተወላጁን እየተንከባከቡት እንደሆነና ተጠቃሚ መሆኑን ለማሳየት በመፈለግ፣ እግረ-መንገዳቸውን ከቀሪው ኢትዮጲያዊ ወገኑ ጋር በመነጠል..ድጋፍ ለማግኘትና በውስጣቸው የተፈጠረውን ቀውስ በዚህ በኩል ቀዳዳውን ለመድፈን የሚደረግ የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ስልት ነው። ..ደግሞስ ሕወሐት “አጋር” ከሚላቸው ብ.አ.ዴ.ን፣ ኦ.ህ.ዴ.ድ.፣ ደቡብ ሕዝቦች ተለይቶ፣ በሕዝብ ገንዘብ ስብሰባ የሚጠራበትና ያሻውን የሚያደርግበት አግባብ ምንድነው?..የሚለው ከዚህ ጋር መታየት ያለብት ነው። ፖለቲካዊ ፍጆታና ማንአለብኝነት በፓርቲው በመነገሱ እንደሆነ ደግሞ ግልፅ ነው።» ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ አሜሪካ ከመጡት ሰባት የሕወሐት ባለስልጣናት መካከል- ማለትም አባይ ወልዱ፣ ብርሃነ ኪ/ማሪያም፣ ተ/ወይኒ አሰፋና ዳንኤል አሰፋ በዋነኛነት ሲጠቀሱ፣ ከሰባቱ ሶስቱ ስብሰባውን ሳያካሂዱ ከቡድኑ ተገንጥለው በአሜሪካ መቅረታቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል። ቤተሰቦቻቸውን ይዘው (ልጆቻቸውን ጭምር) በመምጣት አሜሪካ ጥገኝነት ጠይቀው መቅረትን የመረጡት ባለስልጣናት ውስጥ የሕወሐት ማ/ኮሚቴ አባላት እንዳሉ ያረጋገጡት ምንጮች በቅርቡ ዝርዝሩን ይፋ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።
http://ecadforum.com/Amharic/archives/9589/
 

Sunday, August 25, 2013

Breaking News: በሚኒሶታ ለአባይ ቦንድ ሽያጭ የተጠራው ስብሰባ ሳይጀመር ተበጠበጠ(ዘ-ሐበሻ) በሴንት ፖል ሚኒሶታ የአባይን ቦንድ ለመሸጥ የኢትዮጵያ መንግስት አዳራሽ ተከራይቶ ለዛሬ ኦገስት 25 ቀን 2013 ዓ.ም ከ ቀኑ 2 ሰዓት እስከ ምሽቱ 8 ሰዓት ስብሰባ የጠራ ሲሆን ስብሰባው ከመጀመሩ አንድ ሰዓት በፊት ብጥብጥ ተነሳ።

    

(ዘ-ሐበሻ) በሴንት ፖል ሚኒሶታ የአባይን ቦንድ ለመሸጥ የኢትዮጵያ መንግስት አዳራሽ ተከራይቶ ለዛሬ ኦገስት 25 ቀን 2013 ዓ.ም ከ ቀኑ 2 ሰዓት እስከ ምሽቱ 8 ሰዓት ስብሰባ የጠራ ሲሆን ስብሰባው ከመጀመሩ አንድ ሰዓት በፊት ብጥብጥ ተነሳ።
በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን “ወያኔን አናምንም፤ 2 ሰዓት ብሎ ጠርቶ ስብሰውን ቀድሞ ሊጀምርና ሊነሳበት የታቀደውን ተቃውሞ ሊያከሽፍ ይችላል” በሚል ገና ከጠዋቱ ስብሰባው ይደረግበታል የተባለበት አዳራሽ በር ላይ ሲጠባበቁ ቆይተዋል። ልክ ስብሰባው ሊጀመር 1 ሰዓት ሲቀረው አንድ የስርዓቱ ደጋፊ የሆነ ሰው ካሜራ ይዞ “ከአባይ በፊት ሰብአዊ መብት ይከበር፤ የታሰሩት ይፈቱ” በሚል ለተቃውሞ የተሰባሰበውን ሕዝብ ሊቀርጽ ሲጠጋ ሕዝቡ “ሃገር ቤት ቪድዮ የቀረጻችሁት ሳያንስ እዚህ ልትቀርጹ ነው ወይ?” በሚል ልጁን ክፉኛ ከደበደቡት በኋላ ካሜራውን ሰባብረውበታል ያሉት የአይን እማኞች ወዲያውም ከ20 የሚበልጡ የሴንት ፖል ከተማ ፖሊስ መኪናዎች አካባቢውን በመክበብ ብጥብጡን አርግበውታል።
የሴንት ፖል ፖሊሶች መቃወም ትችላላችሁ፤ ሆኖም ግን ሰውን መደብደብ አግባብ አይደለም በሚል ለተቃውሞ የተዘጋጁትን ሲበትኑ ሕዝቡም “በአባይ ስም የሚደረገው ሕገወጥ ስብሰባ ነው” በሚል ለፖሊስ በማመልከታቸው ፖሊስም የቦንድ ሽያጩ አይደረግም ሲል ቃል ገብቷል።
ሕዝቡ ፖሊስ የቦንድ ሽያጩ ተሰርዟል ቢላቸውም ማረጋገጫ የለንም በሚል በአካባቢው የሚገኝ ሲሆን ብጥብጡን ተከትሎ በሴንት ፖል ፖሊስ ታስረው የነበሩት ኢትዮጵያውያን ወዲያው ተለቀዋል።
የኢሕአዴግ መንግስት በሚኒሶታ የአባይ ቀን በሚል ቦንድ ለመሸጥ የተከራየው የላኦ ኮምዩኒቲ አዳራሽ አድራሻ 320 University Ave W St Paul, MN 55103 ነው።
ዘ-ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎችን ከፎቶ ግራፍ እና ቪድዮዎች ጭምር ይዛ ትመለሳለች።
ይጠብቁን፤ ይመለሱና ይመልከቱን።
Short URL: http://www.zehabesha.com

በሀይማኖት ሽፋን የወያኔ የፖለቲካ አጀንዳን ማራመድ ይቁም!

August 25, 2013

አምባገነኑ የህውሃት ኢህአዲግ አገዛዝ አገራችን ኢትዮጵያን ላለፉት ሀያ ሁለት አመታት በጎሳ በቋንቋና በሃይማኖት ለመከፋፈል ሆድ አደር ተላላኪዎቹን አስርጎ በማስገባት ዜጎችን እርስ በርስ በመከፋፈል ሰይጣናዊ እኩይ አላማውን በማካሄድ ላይ ይገኛል። ጉዳይ አስፈጻሚው የሆኑትን ሆድ አደር ግለሰቦች በሀይማኖት ተቋማት ውስጥ ሳይቀር አስርጎ በማስገባት ይቅር የማይባል ከፍተኛ በደል በመፈጸም ላይ ይገኛል።
እነዚህን ሆድ አደር ወገኖች የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን ጠንቅቆ ሊያውቃቸው ይገባል። ወያኔ በዋልድባ ገዳም እና በመነኮሳቱ ላይ እያደረሰ ያለውን ዘግናኝና አላፊነት የጎደለውን ተግባር ለማውገዝና ከአድራጎታቸውም እንዲታቀቡ የሚጠይቁ ምእማናን የተቃውሞና የተማጽንኦ ጥሪያቸው እንዳይሳካ ለማድረግ ሆድ አደሮቹ ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም፤ አሁን ደግሞ ከአሳዳሪዎቻቸው በሚሰጣቸው መመሪያ መሰረት፦ ጠንካራ እንቅስቃሴና የተቀናጀ የአንድነት ሕዝባዊ ትግል አሁን በጋራ በማድረግ ላይ የሚገኙትን የእስልምና እና የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ምእመናንን አንድነት ለማጥፋት በግራኝ መሀመድ ዘመን የፈረሱ ቤተክርስቲያኖችን ለማሳደስ ገንዘብ አዋጡ በሚል ሰበብ፤ የወቅቱን ሁኔታ ያላገናዘበና ባደፈ ቃላት የተደረተ መሰሪ በራሪ ወረቀት ሰሞኑን እየበተኑ መሆኑን ተረድተናል።
ይህ አፍራሽና ከፋፋይ ተልእኳቸው በቃ መባል ያለበት ጉዳይ ሲሆን፤ በዲሲና አካባቢው የምትገኙ ምእመናንም የነዚህን የወያኔ መራሽ አፍራሽ ተላላኪዎችን ከፋፋይ ሴራ ለማስወገድ በቆራጥነት እንድትታገሉአቸው በልዑል እግዚአብሄር ስም እናሳስባለን። አገራችን ኢትዮጵያን ከበግ ለምድ ለባሽ የቀበሮ ባህታዊያን አምላክ ይጠብቅ።
አገራችን ኢትዮጵያን እና ህዝቧን አምላክ ይባርክ!!!
ከአገር ወዳድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ምእመናን
ዋሽንግተን ዲሲ

Oromo activist, Tesfahun Chemeda, dies in prison while serving life sentence

tesfahunchemeda(OPride) – Engineer Tesfahun Chemeda, a fierce Oromo rights advocate and a former UNHCR recognized refugee, died yesterday of undisclosed cause at Kaliti prison, where he was serving a life sentence under concocted charges of plotting to overthrow government, reports said.

Chemeda was nabbed along with a close friend Mesfin Abebe in 2007 from Nairobi, where they lived as refugees since 2005, by Kenyan anti-terrorism police and was later deported to Ethiopia, according to Oromia Support Group (OSG), a UK-based human rights organization.

“The two men were picked up in a restaurant by Kenyan anti-terrorist police on 27 April 2007 and taken to Kamukunji police station, where they were held overnight before being transferred to Giriri police station,”
OSG wrote in 2010 press release. 
The duo were subsequently visited by UNHCR and members of the FBI in Kenya who assured them that “they would not be deported,” according to OSG reports and activists who were advocating for their release at the time.


“I had an opportunity to meet with Kenyan anti-terrorism head, inspector Francis Wanjiru, and an FBI agent,” wrote Raajii Gudeta, 31, in an email to OPride from Edmonton, Canada where he now lives. “Both the FBI and Kenyan official told me that they [Chemeda and Abebe] were not terrorists. We don’t have any business with them but the Ethiopia government need them badly.”


On May 9, 2007, during a court hearing, Kenyan officials told a local judge the two were already “sent back to Ethiopia to face terrorism charges,” citing a doctored “Laissez Passer from the Ethiopian embassy, dated 1 May, which had obviously been backdated as that day was a public holiday,” according to OSG.

Efforts by members of the Kenyan Oromo community, Kenyan Human Rights Commission, and the UNHCR to prevent their refoulement went to no avail, according to Sori Fengor, 43, of Minnesota, who knew and lived with Chemeda at the time. Chemeda and Abebe were held incommunicado until December 2008 when they were formally charged in Ethiopian court.

“The last time I saw Chemeda was on May 10 2007 at Muthaiga police station,” wrote Gudeta, who worked as a Community Development Officer for the International Rescue Committee at the time. “After I dropped off food and water for them, Tesfahun saw me crying and grabbed a copy of the Daily Nation newspaper and slapped me saying, ‘we will be handed over to the Woyane [Ethiopian] regime, forget about us and focus on organizing the Oromo youth so that the Oromo struggle can reach its final destination.’”

Chemeda was accused of being an activist with the outlawed Oromo Liberation Front (OLF), an organization formed in 1973 to fight for self-determination of Oromo people in Ethiopia. A three-judge panel at Ethiopia’s federal court later
sentenced Chemeda to life in prison without parole in April 2011.

Fifteen other Oromo co-defendants received stiff prison terms while Abebe was sentenced to death. The Oromo are Ethiopia's single largest ethnic group, comprising more than 40 percent of the country's population. There are an estimated 20 to 30,000 Oromo political prisoners in Ethiopia.

Chemeda was born in the East Wollega zone of Oromia region near Guduru district. He attended Shambu High School before joining Addis Ababa University's School of Civil and Environmental Engineering. Following his graduation in 2001 from Addis Ababa University, Chemeda, a civil engineer, worked for Ethiopian Road Transport Authority.

Chemeda sought asylum in Kenya sometime in 2005 following harassment and intimidation at the hands of Ethiopian security and road transport administration officials, his acquaintances said.

Early Saturday afternoon when the news of Chemeda’s death broke on social media, activists changed their profile pictures to his photo and wrote to express their grief and condolences. Many remembered Chemeda as a humble, soft-spoken rational thinker, and strategic leader.

Other acquaintances reached by OPride remembered Chemeda for his relentless advocacy and commitment to Oromo people’s freedom. Many Oromo refugees in Kenya knew him in 2005 and 2006 through his role in the now defunct East African Oromo Students’ Association and efforts to organize Oromo refugees in Kenya.

Chemeda’s involvement in Oromo student activism dates back to early 2000. “I went to Menelik Hospital with Chemeda to collect the corpse of Simee Tarafa, an Oromo student who was mysteriously killed in 2001 while attending Mekelle University in Ethiopia’s Tigray region,” recalled Geresu Tufa.

“Before that I worked closely with Chemeda in a 12-member Oromo students committee set up to organize a nationwide campaign to extinguish a forest fire in Bale and Borana regions.”  Chemeda was instrumental in signing up over 3000 volunteers and about 480 students dispatched to put out the forest fire, according to Tufa.
Chemeda has been in solitary confinement at Kaliti prison for nearly two years after he was transferred there from Ziway, according to family sources. Early reports about the circumstances of his death are unclear. Some suggest that Ethiopian officials murdered him because they could not break his spirit even after years of torture. Others say authorities are unofficially claiming that he committed suicide.

Chemeda’s sister, the only visitor he had seen for years, was denied the body on Saturday pending “further medical examination,” according to Gudeta. She had seen him earlier this week and reported no changes in his attitude or demeanor.


Saturday, August 24, 2013

ኖርዌይ ኤምባሲ እና ኢ/ር ኃይሉ እየተወዛገቡ ነው

    
ኖርዌይ ኤምባሲ እና  ኢ/ር ኃይሉ እየተወዛገቡ ነው
 
“ያከራየኋቸውን ቤት ለመልቀቅ እምቢተኛ ስለሆኑ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቄያለሁ”
- ኢ/ር ኃይሉ
ኖርዌይ ኤምባሲ ከኢ/ር ኃይሉ ሻውል የተከራየውን ባለ ሁለት ፎቅ የመኖሪያ ህንፃ ለ15 አመታት ሲጠቀምበት እንደቆየ የገለፁት የአዲስ አድማስ ምንጮች፣ በሁለቱ ወገኖች መካከል ውዝግብ የተፈጠረው ቤቱን ልቀቅ፣ አልለቅም በሚል ነው ብለዋል፡፡ በ97 ምርጫ የምርጫ ዘመቻ ቅንጅትን በፕሬዚዳንትነት የመሩት ኢ/ር ኃይሉ ሻውል፣ ከኤምባሲው ጋር በነበራቸው የኪራይ ውል መሰረት ከ7 ወራት በፊት ቤቱን እንዲያስረክባቸው እንደጠየቁ ተናግረዋል፡፡ በ3200 ካሬ ሜትር ግቢ ውስጥ የተሰራው ባለ ሁለት ፎቅ መኖሪያ ህንፃ በ1200 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ነው፡፡
ቤቱን ስለምንፈልገው ልቀቁልን በማለት ከሰባት ወራት በፊት በደብዳቤ ብንጠይቅም፤ ኤምባሲው ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም የሚሉት ኢ/ር ሃይሉ፣ ከአንድ አመት በፊትም ኤምባሲው ቤቱን እለቃለሁ ቢልም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል ብለዋል፡፡ “ቤቱን በትክክል ከፈለጋችሁት ግዙን” በማለት ለኤምባሲው አማራጭ አቅርበው ተቀባይነት እንዳላገኘም ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ጉዳዩን ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማሳወቃቸውን ኢ/ር ኃይሉ ጠቅሰው፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱም ኤምባሲው ቤቱን እንዲለቅ ጥያቄ አስተላልፏል ብለዋል፡፡
“ህግና ስርዓትን ተከትዬ ቤቱን እንዲለቁ በትዕግስት ጠብቄያለሁ፡፡ እምቢ ካሉ በግል ንብረቴ ከእነርሱ ጋር እንካ ሰላንቲያ አልገጥምም” ያሉት ኢ/ሩ፤ ጥቁርን በመናቅና በማን አለብኝነት የሚካሄደውን ህገወጥነት ፈፅሞ አልቀበልም ብለዋል፡፡ ኤምባሲው የያዘብኝ ቤት ከመኖሪያ ቤቴ ጋር በአጥር ስለሚገናኝ በቤቴ በኩል አፍርሼ በመግባት ግቢውን ለማስተካከል ወስኛለሁ ብለዋል ኢ/ር ኃይሉ፡፡ ወደ ኤምባሲው በተደጋጋሚ ደውለን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ምክትል አምባሳደሯን ለማነጋገር ብንሞክርም “አሁን ቴሌ ኮንፈረንስ ላይ ነኝ፤ ማናገር አልችልም” የሚል ምላሽ በፀሀፊያቸው በኩል ተናግረው፤ መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡
ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፕሮቶኮል ክፍል ደውለን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ሀላፊ ለማግኘት ሙከራ ብናደርግም ለስብሰባ ከግቢ ውጭ ናቸው በሚል ምላሽ ልናናግራቸው አልቻልንም፡፡
addis admas

The Totolamo-Kofele blood bath victims named, death toll still climbing

August 24, 2013
The Horn Times update August 24, 2013
by Getahune Bekele-South Africa

“Wolahi, Wolahi…” swears 85 year old Totolamo village barley farmer and cattle herder Hajji Abdinur Shifa when a reporter asked him if he know any terrorist hiding in his village. His face looks like a paint of sorrow and grief. His wife affectionately called by the villagers, Adiyo, was too fragile to talk about the August 3 2013 blood bath that turned their agriculture and livestock rich village into an inferno.Totolamo-Kofele blood bath victims named
“My son took three bullets and died a day later at Sashemene general hospital. The body that was weakening by fasting could not respond well to treatment and he succumbed to his wounds without saying goodbye. His killers (federal police commandos) did not allow us entry to the hospital. My son Abdulkarim is dead but he will live in my heart until I join him in paradise…,” the respected elder said wiping his tears with a piece of garment.
On that fateful day, 3 August 2013, Abdulkarim Abdinur Shifa, 39, was at Erob Gebeya mosque loading onto his van sacks of barley, corn, and potato donated by farmers to be distributed among the needy in the city of Sashemene for Eid celebration.
When he was about to leave, bullets started raining down and the scream of women and children filled the salubrious air of Totolamo. Tigre people Liberation Front gunmen in police uniform massacred eleven people including an elderly imam and an infant.
The tragedy touched every household from Totolamo to Kofele in southwest oromyya.
In the land famed for its sylvan beauty, despite the aroma of ripe corn, the stench of death still hangs in the air. The approach of the delightful month of September did not lift the gloom of the August blood bath. According to our sources from Sashemene general hospital, currently the death toll stands at sixteen- all Muslims and close relatives.
The Horn Times manage to obtain the names of 14 victims of the August 3 slaughter…
1. Adam Jamal
2. Lenco Jilcha
3. Habib Wabe
4. Gachano Tuse
5. Muhammad Debel Ouse
6. Jamal Arsho Arsi
7. Muhammad Eidao
8. Amman Buli
9. Muhamud Hassan
10. Rashid Burka
11. Abush Ebrahim
12. Mamush Ebrahim
13. Tuke Besso
14. Abdulkarim Abdinur Shifa

Furthermore, two hundred young men arrested on 3 August 2013 are still languishing in Kofele town police prison without any charge.

http://ecadforum.com/News/
infohorntimes@gmail.com

የወጣቱ የመጥለፍ ፖለቲካ በ” ይልቃል አዲሱ ልደቱ…? ” ፀሁፉ ውስጥ

በጥያቄ ምልክትና እና በቃለ አጋኖ የታጀበውን ‘’ይልቃል አዲሱ ልደቱ” በሚል ርዕስ ወጣት ዳዊት ስለሞን በብዕር ስም /አይናለም/ የተፃፈውን ባለ ብዙ ሀሳብ ፅሁፍ አነበብኩት ፡፡ አንድ ፅሁፍ ሲፃፍ አንባቢ ሊታዘብ ይችላል ሰለዚህ እውነት ላይ እና እየታዩ ካሉ ነባራዊ ሁኔታዎች አንፃር መቃኘት አለበት የሚለው ዋና ጉዳይ በዚህ ፀሁፍ ውስጥ ለኔ አልታየኝም ፡፡ በፅሁፉ ውስጥ አንባቢን ለማሳመን የተደረጉ ውጣ ውረዶች ከመጥቀሴ በፊት ፀሀፊው አባል በሆነበት አንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ውስጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተመለከትኩትን የሚበረታታ ጉዳይ ከማሳሰቢያው እጠቅሳለሁ፡፡
ማሳሰቢያ ‘’ይልቃል አዲሱ ልደቱ” ፅሁፍ ፀሀፊ ዳዊት ሰለሞን የአንድነት ፓርቲ ልሳን የሆነው ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ኣዘጋጅ ለመሆኑ አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የአንድነት አባል ስለነገረኝ ከዚህ በታች የምጠቀመው የብእር ስሙን ሳይሆን ዳዊት የሚለውን ዋና ስሙን መሆኑን አሳውቃለሁ፡፡
መኢአድ ሲባል ኢ/ር ሀይሉ ሻወል፣ ደቡብ ህብረት ሲባል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ፣ ኦብኮ ሲጠቀስ ዶ/ር መረራ ጉዲና… የፖለቲካ ተክለ ሰውነት ለብሰው ብቅ ይሉብናል፡፡ ይህ የፖለቲካ ተክለ ሰውነት በአንድት ውስጥም ግዝፈቱን ሳይቀንስ ተንሰራፍቶበት ቆይቷል፡፡ ይህ ማለትም አንድነት ሲባል በየደቂቃው የሚለዋወጥ አቋም ያለው ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው እና ባለመልካም ባህሪው ዶ/ር ሀይሉ አርአያ ድቅን ይሉብን ነበር እነአቶ አስራት ጣሴን አስከትለው፡፡ ወጣት ዳዊትም በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ የሚታዩ ችግሮች ብለው ከጠቀሱዋቸው መካከል የግለሰብ ተክለ ሰውነት መገንባት አንዱ ነው፡፡
እኔም የግለሰብን ተክለ ሰውነት አንዱ መስፈርት አድርጌ ፓርቲዎችን ስገመግም አንድነት አሁን ካሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ውስጥ የተሻለ ነው እንድል ያደረገኝ ከግለሰብ ትከሻ ላይ ወርዶ አበረታች የሚባል የቡድን ስራ ማክናውን ላይ በመሆኑ ነው፡፡
የተመለከትኩትን ጠንካራ ጎን ከገለፅኩ በኋላ የፓርቲው አባል የሆኑት ወጣት ዳዊት ፅሁፍ ላይ ላተኩር፡፡ ሀሳብን በነፃነት ለመግለፅ ያደረገውን ጥረት በማድነቅ ፅሁፉ መጀመሪያ ላይ የጠቀሱት የደርግ/ የኢህአፓ /የመኢሶን ፖለቲካዊ መጠላለፍ ዛሬ ላይ እንዲመጣ ወይም ዛሬ ላይ ያለው የመፈራረጅ ፖለቲካ እንዲቀጥል ታጥቀው የተነሱ ነው የሚመስለው፡፡ እንዴት! ማለት ጥሩ….. በአዲስ መስመር ከመቀጠሌ በፊት እኔ የሰማያዊ ፖርቲ አባልም ደጋፊም አለመሆኔ ሊታወቅ ይገባል፡፡
አንባቢን ለማሳመን እና ሰማያዊ ፓርቲ የወጣቶች ስብስብ መሆኑን ለማጣጣል የአቶ ልደቱ ወጣት መሆን በመጥቀሥ በጥሩ ሁኔታ እየተቀሰቀሰ ያለውን ፖለቲካ ለመጥለፍ ‹‹አዲሶቹ ጎጆ ወጪዎች ከመጀመሪያው ቤታቸው ሲወጡ በአብዛኛው ባዶ እጃቸውን አይሆኑም፣የእናት ፓርቲያቸውን የፖለቲካ ፕሮግራም፣አደረጃጀትና አባል ይዘው ሹልክ ይላሉ፡፡ለዚህ እንደምሳሌ ኢዴፓና ሰማያዊ ፓርቲን መውሰድ ይቻላል፡፡›› ይሞክራሉ፡፡ እኔም አንድ የመጥለፉ መንገድ ልከተልና ፀሀፊውን ልጠይቀው፡፡ ቅንጅት የአራት ፓርቲዎች ጥምረት ነው፡፡ መሪዎቹ ታስረው ሲፈቱ በጋራ መቆም አቃታቸውና የየራሳቸውን ደጋፊና አባል በመያዝ ለአራት ተሰነጣጠቁ፡፡ከግንቦት 7 በስተቀር ሁሉም የሰላማዊ ትግል መርጦ የቅንጅቱን መንፈስና ፕሮግራም ለማስቀጠል በያለበት ይንቀሳቀሳል፡፡ ከነዚህ ውስጥም አንድነት አንዱ በመሆኑ የእናት ድርጀቱን አባል ፕሮግራም ይዞ ሹልክ አለ ማለት ነው ወይስ አንድነት የተለየ ፕሮግራም አረቀቀ? ይህን ለመመለስ የቅንጅትንም የአንድነት በደንብ ፕሮግራሞች ማየት ያስፈልጋል እንዳትረሳው!
የሰማዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር ላይ ያስቀመጠው ቅሬታ / ግን ሰይጣናዊ ቅናት ብለው በትክክል ይገልፀዋል/ ጠቅለል አርጌ ለመግለፀ በሁለት መክፈል እፈልጋለሁ፡፡ ሊቀመንበሩ ላይ የቀረበው ቅሬታ ለፖለቲካው በማሰብ በሚል እና ፀሀፊው ጎልቶ ለመውጣት ባለው ጉጉት የሚከተላቸው መንገዶች በሚሉ ፡፡
ለፖለቲካው በማሰብ
ኢ/ር ይልቃል /የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር/ “ፓርቲዎች አሉ ብለን አናምንም ተባበሩ የምትለን ከማን ጋር ነው ? መድረክ ምን ሰራ አንድነትና መድረክ እየተባሉ አይደለም? አንድነት ውስጥ የገባው ብርሃን ወጥቷል እኛ ከማን ጋር እንተባበር ? ብለዋል ብሎ ወጣት ዳዊት ይኮንናል፡፡ የኢ/ር ይልቃል ንግግር ላይ ያለውን ስህተት ለማሳየት ፓርቲዎቹ የሰሩትን ምንም መረጃ ማቅረብ ስላልቻለ በደፈናው በህብረት ለመስራት አንፈልግም ብለዋል ሲል ተንከባሎ ያልፋል፡፡ የመድረክ አባል ፓርቲዎች የደቡብ ህብረት ከፕ/ር በየነ ሳምሶናት ውስጥ መውጣት ሳይችል፣ ኦፍዴን ከአቶ ቡልቻ የግል ንብረትነት ሳያልፍ፣ ኦብኮ ከዶ/ር መራራ የኮሜዲ ምሽት ሳይላቀቅ ፣አረና አባላቱ በነፃ ዝውውር ለሰማያዊ ፓርቲ እየፈረሙ ባሉበት ሰአት እና አንድነት በኣዛውንቶችና በወጣቶች መሀክል በሚደረግ ገመድ ጉተታ ፖለቲካ ውስጥ ነው ያለው ስለዚህ ከማን ጋር በህብረት ይስራ ነው የሚባለው፡፡ በተጨማሪም ብርሀንም ከአንድነት የወጣው ገመድ የጉተታ ውጤት ይዞት የሚመጣው ጦስ አስግቶት ነው፡፡ ታዛቢ ስላለ እውነቱ ይህ መሆኑን መግለፅ ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ የተቀረበው ቅሬታ ለፖለቲካው በማሰብ አደለም ለማለት እደፍራለሁ፡፡
በተጨማሪም አንድነትን ጨምሮ ሁሉም የመድረክ ፓርቲዎች ጥርት ያለ የፖለቲካ ፕሮግራም ስለሌላቸው መስማማት አልቻሉም ፡፡ ይህንን ስል በስሜት አለመሆኑን ለማስገንዘብ ሁለት ምሳሌ ልጥቀስ፡፡ የመሬት ጥያቄና የመገንጠል መብት ፓርቲዎቹ ከግንባርነት እንዳያልፉ ማነቆ ሆነው ስራ እዳይሰሩ ያደረጋቸውን ብቻ ማንሳት በቂ ነው፡፡ ይህም እውነት ሲገለጽ በሰማያዊ ፓርቲ ፕሮግራም ላይ የተቀረበው ቅሬታ ለፖለቲካው በማሰብ አይደለም ለማለት እገደዳለሁ፡፡
ጎልቶ ለመውጣት የሚደረግ ጥረት
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንድነት ከላይ እንደጠቀስኩት ከግለሰብ ስብእና ራሱን በማፅዳት የቡድን ስራን በመጀመር የሚያበረታታ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ ይህም የቡድን እንቅስቃሴ ባለፉት ግዚያት እንደተመለከትነው በተለያዩ የክልል ከተሞች በመንቀሳቀስ የቀዘቀዘው የህዝብ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ዳግም እንዲያንሰራራ ሚዛን የሚደፋ አስተዋፆ አድረጓል፡፡ ለዚህም አበረታች ጅማሮ ከፊትም ከኋላም በመሆን ከፍተኛ አስተዎ ያደጉትን ግርማ ፣ዳንኤል እና በላይን የመሰሉ ወጣት ፖለቲከኞችን ማመስገን ያስፈልጋል፡፡ በዛውም ልክ ይልቃል ጎልቶ ለመውጣት ይፈልጋል ተብሎ እንደተከሰሰው በአንድነት ህዝባዊ ንቅናቄም ውስጥም በበርካታ ወጣቶች ላይ ጎልቶ የመታየት ፍላጎት ሲከሰት ከርሟል፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዱ ወጣት ዳዊት ይግኝበታል፡፡ እንዴት የሚል ጥያቄ ከተነሳም መልሱን ክዚህ በፊት ወጣቱ የሚያድጋቸውን ጎልቶ ለመውጣት የሚደረግ ድርጊቶች ላሳይ፡፡ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አንድነት ፓርቲ ውስጥ የተመለከታቸውን ህፀፆች እንደጋዜጠኝነቱ እንዲታረሙ በበሳል ብእሩ ሲጠቁም የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የጋዜጠኛውን ጥቆማ በመቀበል የታዩትን ችግሮች ለማረም ደፋ ቀና ብለዋል፡፡ ነገር ግን ፍየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ የተባለው ብሂል በወጣቱ ዳዊት ላይ ተተግብሮ ‹‹ ተመስገን ደሳለኝ ሲያዳልጠው›› በሚል ጽኁፍ በአደባባይ ፓርቲውን ለምን ነካ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ በማለት እፍኝ እውቅና ለማግኘት ሲታገል መድከሙ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡ ይህ ተግባር በተመስገን ላይ ብቻ የተገደበ እይደለም ፡፡ ብዙ መጥቀስ ይቻላል ነገር ግን ዝም በመባሉ ያሸነፈ ስለመሰለው በተመሣሳይ ላሞኛችሁ አይናችሁን ጨፍሁ ብሎ በኢ/ር ይልቃል ላይ እንዲህ ሲዘምት ጎልቶ ለመውጣት በሚደረግ ጥረት የሚቀዘቅዘው የወጣቶች የፖለቲካ ተሳትፎ ስላሳሰበኝ ነው ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ የተገደድኩት፡፡
በአጠቃለይ የወጣቱ ፅሁፍ ለሀገራችን ፖለቲካ በማሰብ የቀረበ ሀሳብ ሳይሆን ጎልቶ ለመውጣት የሚደረግ ጥረት በመሆኑ የተጀመረው የህዝብን የማንቃት ስራ አዳክሞ ሀገሪቱን በአንባገነንነት ለሚመራው ኢህአዴግ ነው የሚጠቅመው፡፡ ስለዚህ ወጣት ዳዊት ገና ብቅ ብቅ የሚሉ ወጣት ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኛ ተመስገን ላይ በመፃፍ እውቅናን ለማግኘት ከመጣር ከላይ በአንድነት ውስጥ ከባድ እንቅስቃሴ እያደረጉ ያሉትን ምሳሌ በማድረግ ስራቸውን ማጉላት ላይ ብታተኩሩ ወይንም እነሱ ልምድ ካላቸው ፖለቲከኞች ጀርባ ሆነው ልምድ ቀስመው ዛሬ ለሀላፊነት የበቁበትን መንገድ መከተል በሳልነት መሆኑን ሳልጠቁም አላልፍም፡፡ በመጨረሻም ሰማያዊ ፓርቲ አዲስ መስመር…
ምስረታ ጀምሮ አወዛጋቢ የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ 8 አመት ሙሉ የቀዘቀዘውን የሀገሪቱ ፖለቲካ ሚዛን በሚደፋ መልኩ ለማሞቅ ( ለማንቀሳቀስ) ጥረት እያደረገ ነው፡፡ ነገር ግን የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም እና በፓርቲው ውስጥ ያሉት አመራሮች ከሊቀ መንበር ውጪ ያላቸው የፖለቲካ ብስለት በሰፊው ለህዝብ ስላላደረሰ አውዛጋቢነቱ እንዲቀጥል አድርጎታል ፡፡ ይህም የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም እንዲሁም በፓርቲው ውስጥ ያሉት ወጣት አመራሮች ያላቸው የፖለቲካ ብስለት ለሰፊው ህዝብ ካልደረሰ በሀገራችን ለዘመናት ለቆየው የመጠለፍ ፖለቲካ ጭዳ ይሆናል ባይ ነኝ፡፡ በተጨማሪም እንታገልለታለን ለምትሉት ህዝብ የማሳወቅ ፓርቲው ግዴታም አለበት፡፡

Sport: ሙስሊም ተጨዋችና እግርኳስ

ከሊሊ ሞገስ 
(በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 54 ላይ ታትሞ የወጣ)
ፓፒስ ዴምባ ሲሴ ሃይማኖቱን አ ጥባቂ ሙስሊም ነው፡፡ እስልምና ደግሞ ወለድን መብላት ይከለክላል፡፡ የወለድ ስርዓት ያለበት የፋይናንስ አሰራር ውስጥ ተከታዮቹ እጃቸውን እንዳያስገቡ ይደነግጋል፡፡ ኒውካስል ዩናይትድ wonga ከተባለው ኩባንያ ጋር የማሊያ ላይ ስፖንሰርሺፕ ስምምነት መፈራረሙ ለሲሴ አመቺ አልሆነም፡፡ ኩባንያው የአጭር ጊዜ ብድር የሚሰጥና ከፍተኛ ወለድን የሚጠይቅ ኩባንያ ነው፡፡ ኒውካስል ደግሞ የሲሴ ቀጣሪና ደመወዝም ይከፍለዋል፡፡ የሲሴ እምነት ደግሞ ከwonga ጋር ምንም አይነት የስራ ግንኙነት መፍጠርን አይፈቅድም፡፡ በዚህ ላይ በጨዋታዎች ላይ የኩባንያው አርማ የሰፈረበትን ማሊያ ለብሶ የመጫወት ግዴታ አለበት፡፡
የተጨዋቹ ተቃውሞ ከመነሻው ጠንካራ ነበር፡፡ ማሊያውን አልለብስም በሚለው አቋሙ መጽናቱን ለማሳየት ክለቡ ለቅድመ ውድድር ዘመን ዝግጅት ወደ ፖርቹጋል ያደረገው ጉዞ አካል አልሆነም፡፡ ጓደኞቹ ወደ ዝግጅት ሲጓዙ ሲሴ ቀርቶ ከቤተሰቦቹ፣ ከጓደኞቹና ከሃይማኖት ሊቃውንት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ መከረ፡፡
በዚህ መልኩ ተቃውሞን ሲያቀርብ ሲሴ የመጀመሪያው እግርኳስ ተጨዋች አይደለም፡፡ በ2006 ለስፔኑ ሲቪያ በሚጫወትበት ጊዜ ፍሬዲሪክ ካኑቴ 888.com የሚል ፅሑፍ የሰፈረበትን ማሊያ እንደማይለብስ አስታውቋል፡፡ የኢንተርኔት ቁማር ኩባንያ በመሆኑ ነው፡፡ እንደ ሲሴ ሁሉ የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነው ካኑቴ ደግሞ ይህን በማድረግ የመጀመሪው ስፖርተኛ አልነበረም፡፡ ሃሺም አምላ የተሰኘው ደቡብ አፍሪካዊ የክሪኬት ተጨዋች castle lager የተሰኘውን ቢራ ጠማቂ የኩባንያ ዓርማ የሰፈረበትን መለያ ከመልበስ ታቅቧል፡፡
እስልምና በምንም አይነት መጠን ቢሆን አልኮልን መጠጣትንም ሆነ ለሌሎች እንዲጠጡ ማበረታትን ይከለክላል፡፡ እናም አምላ ከማሊያው ላይ ምልክቱ እንዲነሳለት ጠይቋል፡፡ አስተዳዳሪውም የስፖርተኛውን ጥያቄ ተቀብለው በጨዋታ ላይ አምላ ማስታወቂያ ያላፈረበትን ማሊያ ለብሶ ተጫውቷል፡፡



የሲሴ ጥያቄ የአምላ አይነት ተቀባይነት አላገኘም፡፡ ዘግይቶም ማሊያውን ለመልበስ ወስኗል፡፡ ይሁን እንጂ ሲሴ አቋሙን የቀየረበት ምክንያት ዝርዝር አልታወቀም፡፡ ይልቅ ከፖርቹጋል ዝግጅት በቀረበት ሰዓት የብሪታኒያ ጋዜጦች ተጨዋቹ በካዚኖ (የቁማር ማዕከል) ሳለ የሚያሳይ ፎቶግራፍ በአምዶቻቸው ላይ አትመው ነበር፡፡ ፎቶው ሴኔጋላዊው ቁማሩን ሲጫወት ባያሳዩም ከመቆመሪያው ጠረጴዛ አጠገብ (በሚጫወት ሰው ሁኔታ) ተቀምጦ ነበር፡፡ ቁማሩን ተጫውቶ ከሆነ ማሊያውን ላለማድረግ የነበረው አቋም ከልብ አይደለም የሚሉ አስተያየቶች ተሰንዝረውበታል፡፡ ሆኖም የተጫዋቹ ወኪል ‹‹ሲሴ ቁማርተኛ አይደለም›› ሲል ማስተባበያ ሰጥቶለታል፡፡ የካዚኖው ኩባንያ ቃል አቀባይ ግን ሲሴ ከአንድ ጊዜ በላይ ወደ ቁማር ቤት ለመምጣቱ ማረጋገጫ ሰጥቷል፡፡ በቁማር ቤት መገኘቱን እንጂ ቁማር መጫወቱን ግን አልገለፀም፡፡
የኒውካስል ከተማ ከንቲባ ዲፑ አሃድ ሲሴ ማሊያውን አልለብስም ባለበት ሰዓት ላይ ለተጨዋቹ ድጋፋቸውን ሰጥተው ነበር፡፡ በኋላ አቋሙን መቀየሩ ግን ሰውየውን ለትችት የዳረጋቸው ይመስላል፡፡ በተለይ በቁማሩ ቤት የመገኘቱ ዜና ከንቲባውን አበሳጭቷቸዋል፡፡ አሃድ ለቢቢሲ በሰጡት መግለጫ እንዲህ ብለዋል፡፡ ‹‹በድርጊቱ በጣም አፍሬያለሁ፡፡ እኔ ብቻ ሳልሆን በአቋሙ የደገፉትን ሁሉ አሳፍሯል፡፡ በቁማር ቤት መገኘቱ (ቁማር ባይጫወትም እንኳን) መጥፎ መልዕክት ያስተላለፈ ይመስለኛል››
ለሃይማቱ ተከታዮች ፆም ሌላው ግዴታ ነው፡፡ ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያ ድረስ ከምግብ፣ መጠጥ፣ ማጤስ እና ወሲብ መፈፀም መራቅ ግድ ነው፡፡ በረመዳን ወር ሙስሊሞች በዚህ ይተጋሉ፡፡ ወቅቱ የፀሎት ጊዜም ነው፡፡ በዚህ ወር ሙስሊሞች ከበዛ መዝናናት ሳይቀር ይታቀባሉ፡፡
ለስፖርተኞች ደግሞ ፈታኝ ጊዜ ነው፡፡ አንዳንዶች ጭራሹኑ አይጾሙም፡፡ ሌሎቹ ደግሞ የመጣውን ሁሉ ተጋፍጠው ይፆማሉ፡፡
ከማይፆሙት መካከል አንዱ ኒኮላ አኔልካ ነው፡፡ በፆም ወቅት ጉዳት እንደሚደራረብብኝ አረጋግጫለሁ ያለው ፈረንሳዊ የማይፆምበትን ምክንያት አቅርቧል፡፡ አንዳንድ አሰልጣኞች ደግሞ ተጨዋቾቻቸው እንዳይፆሙ ይከለክሏቸዋል፡፡ እንደማሩዋን ሻማክ ያሉት ደግሞ የአሰልጣኞችን ትዕዛዝ ወደ ጎን በማለት የሃይማኖታቸውን ግዴታ ይወጣሉ፡፡ በአንድ ወቅት ካኑቴ ሲናገር ‹‹በፆሙ ወቅት የማደርገውን ሁሉ የቡድን ጓደኞቼ በአንክሮ ይከታተላሉ›› ብሏል፡፡ ይከታተሉ እንጂ በፀሎቱ ጊዜ አይረብሹትም፡፡ እምነቱን ያከብሩለታል፡፡ ‹‹ስለዚህ እየጾምኩኝ መጫወቴ የተለመደ ነው›› ይላል፡፡
ሙስሊም ተጨዋቾች በረመዳን ወር በተቻላቸው መጠን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ቢገደቡላቸው አይጠሉም፡፡ ፆሙን በአግባቡ ለመፆም ሲሉ ነው፡፡ በአብዛኛው በሙስሊሞች የተገነባ ቡድን ያለው የግብፁ አል አህሊ ክለብ ጥሩ ምሳሌ ነው፡፡ የካይሮው ክለብ በአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ከኦርላንዶ ፓይሬትስ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ከሐምሌ 28 ወደ ነሐሴ 3 ቀን 2005 እንዲቀየርለት ጠይቆ የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን ጥያቄውን ተቀብሎ ቢሆን ኖሮ ጨዋታውን ከፆሙ መጠናቀቅ በኋላ ይደረግ ነበር፡፡ ሆኖም ካፍ ጨዋታው በተያዘለት መርሐ ግብር እንዲቀትል (እንዳይቀየር) ወስኗል፡፡
አፍሪካዊያን እግርኳስ ተጨዋቾች ሁሉ ሙስሊሞች አይደሉም፡፡ ወይም ሙስሊም ተጨዋቾች ሁሉ አፍሪካዊያን ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ግን የአፍሪካዊያን ሙስሊም እግርኳስ ተጨዋቾች ቁጥር ብዙ ነው፡፡
muslimpopulation.com እንደተሰኘው ድረገፅ መረጃ ከሆነ ከግማሽ በላይ አፍሪካዊያን የእስልምና እምነት ይከተላሉ፡፡ ለእንግሊዝ አገር ሙስሊም ተጨዋቾች ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመወጣት እንዲጫወቱ ለማድረግ ድጋፍ ሰጪ ተቋም አላቸው፡፡ ቀድሞ ያልነበረውን ይህን አገልግሎት የሚሰጠው ተቋም በ2011 ናታን ኤሊንግተን በተባለ የክሪው አሌክሳንድራ አጥቂ የተመሰረተው የሙስሊም ተቋም በ2011 ናታን ኤሊንግተን በተባለ የክሪው አሌክሳንድራ አጥቂ የተመሰረተው የሙስሊም እግርኳስ ተጨዋቾች ማህበር ነው፡፡ በሊቨርፑሉ የስፖርት ህክምና ቡድን ኃላፊ ተጨዋቾች ምን ማድረግ እንዳለባቸው ምክር ይሰጣል፡፡ በማፍጠሪያ ሰዓት ጥቂት ብቻ እንዲመገቡና በኋላም በዛ ያለውን ምግብ እንዲያስከትሉ የዶክተሩ መመሪያ ይመክራል፡፡ በተጨማሪም ማህበሩ ከቢቢሲ ጋር በመተባበር ‹‹THE MUSLIM PREMIER LEAGUE›› የተሰኘ ጥናታዊ ፊልም ለማዘጋጀት እየሰራ ይገኛል፡፡ ፊልሙ በእንግሊዝ ከፍተኛው የእግርኳስ ዲቪዚዮን ውስጥ ሙስሊም ተጨዋቾች የሚገጥማቸውን ጉዳዮች ይዳስሳል፡፡ በ20 ዓመቱ የሊግ ታሪክ ሊጉ በሙስሊም ተጨዋቾች ላይ ያሳደረውን አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ ሁሉ በፊልሙ ላይ ይዳስሳል፡፡
Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=6641

“አገራችንን በእርቅ እንታደጋት” ዶ/ር ተጋ

“እውነተኛ እርቅ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን” የሚሉት ዶ/ር ተጋ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ በመረዳት አገራችን ከምትገኝበት አደጋ መታደግ የሁሉም ዜጋ ግዴታ እንደሆነ አመልክተዋል። በማያያዝም በደል ሲበዛ ህዝብ እንደሚያምጽ በመጠቀስ ሳይረፍድ ሁሉም ወገኖች ለእርቅ ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ጠይቀዋል።
እርቅና ሰላም ለማውረድ የሚችሉ ዜጎች አድፍጠው መቀመጣቸውን የጠቆሙት ዶ/ር ተጋ “የፖለቲካ መናኞች” ያሉዋቸውን እነዚህ ዜጎች ከተደበቁበት በመውጣት ባገራቸው ጉዳይ ተሳታፊ ሊሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል።
እውነተኛ እርቅ ቢጀመርና፣ ለማስታረቅ የሚመጥን ስብእና ያላቸው ወገኖች የሚካተቱበት አስታራቂ ቢሰየም ህዝብ እውቅና ለመስጠት እንደማይቸገር ያስታወቁት ዶ/ር ተጋ “ከኢህአዴግ ወገን እርቅ የሚፈልጉና ለልቡናቸው የቀረቡ ሰዎች አሉ። እነሱም ሰው ናቸውና ሰላም ይፈለልጋሉ። ራሳችሁን መናኝ ያደረጋችሁ ከተደበቃችሁበት ውጡና ኢትዮጵያን እናድን” ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል። ሙሉ ቃለ ምልልሳቸው እንደሚከተለው ተቀናብሯል።
ጎልጉል፦ በተደጋጋሚ ስለ እርቅ ይናገራሉ። በርግጥ መፍትሔ ይኖረዋል?ዶ/ር ተጋ፦ ከእርቅ ውጪ ምንም አማራጭ የለም። አለ?
ጎልጉል፦ አሁን ኢህአዴግ ከያዘው አቋም አንጻር “እርቅ ዋጋ የለውም” የሚሉ አሉ፤ዶ/ር ተጋ፦ ስለነዚህ ወገኖች በተለይ የምለው ነገር የለም። በኔ እምነት እርቅ፣ ትክክለኛው የእርቅ መንገድ ተሞክሯል የሚል እምነት የለኝም። ስለዚህ ትክክለኛው እርቅ፣ እውነተኛው አርቅ መሞከር አለበት። እኔ እንደምረዳው ከሁሉም ወገን ትክክለኛ እርቅ ከቀረበ ተቀባይ የማይሆንበት ምክንያት የለም።
ጎልጉል፦ትክክለኛ እርቅ ሲሉ ምን ማለትዎ ነው?ዶ/ር ተጋ፦ ከፍቅርና የሚመነጭ ፍርሃት ሰዎች አምነው እንዲገዙ ያደርጋቸዋል። ፍርሃት ስል አምነው ለሰየሙት መንግሥት ክብር መስጠትና መገዛትን ነው። በሌላ በኩል ደግሞ መሳሪያ ያላቸውና ህግ ያረቀቁ ክፍሎችም ህዝብን መግዛት ይችላሉ። እነዚህ ክፍሎች እኔን ምሰል። እኔ የምልህን አድርግ። አንተ ቦታ የለህም። የአንተ ድርሻ መገዛትና መገበር ብቻ ነው። አንተ ዝም ብለህ ከመገዛት ውጪ ሌላ ተግባርና ድርሻ የለህም በማለት በጉልበት ይገዛሉ። ልክ አሁን እንደሚደረገው ማለት ነው። በሌላ ወገን “አማራጭ ነን”  ብለው በጉልበት እየገዛ ያለውን ለመገልበጥ የሚታገሉ አሉ። ገለልተኛ ሆነው የሚኖሩና የሸሹ ወገኖች አሉ። እነዚህ የሸሹ ሰዎች “የፖለቲካ መናኞች” ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ ሌሎችንም አካትቶ ለመታረቅ ሲስማሙ ትክክለኛው እርቅ ይመጣል። ሳይሞከር አይሳካም ማለት አይቻልምና እንሞክረው።
ጎልጉል፦ ያልተቻለው እኮ እነዚህን ወገኖች ማሰባሰብ ነው? በተለይም ኢህአዴግን ወደ እርቅ የሚገፋው ጉዳይ የለም የሚሉም ወገኖች አሉ። ኢህአዴግ ምን አስፈርቶት ወደ እርቅ ይመጣል? የሚሉ አሉ፤ዶ/ር ተጋ፦ ለጊዜው ሃይል አለኝ ብሎ ከተራራ ላይ አልወርድም። መሳሪያ አለኝና እርቅ አይበጀኝም። ጡንቻ አለኝና ሰላም አያሻኝም በማለት ኢህአዴግ የሚያከር ከሆነ የተጎዱ፣ የተረገጡ፣ የተገፉ፣ የከፋቸው፣ የባሰባቸው ቀኑ ሲደርስ “አታስፈልግም” ብለው ይነሳሉ። ዓለም ብዙ አሳይታናለች። የህዝብ ቁጣ ሲነሳ የሚደርሰው አደጋ የከፋ ነው። እኔን ዘወትር የሚያስጨንቀኝ ይህ ነው። የኢህአዴግ ሰዎችም ቢሆኑ ሰዎች ናቸውና ከደጋፊዎቻቸው ጭምር ይህንን ሳያስቡት ውለው ያድራሉ ብዬ አላስብም። ደግሞም ያስባሉ። እንደውም ከማንኛቸውም በላይ የኢህአዴግ ደጋፊዎች እውነተኛ እርቅ የሚመኙበት ወቅት ላይ ለመሆናቸው ጥርጥር የለውም። ዋናው ጉዳይ ግን እንዴት …
tegga
ዶ/ር ተጋ ለንዳዶ
ጎልጉል፦ ኢህአዴግ እርቅ ይፈልጋል እያሉ ነው?ዶ/ር ተጋ፦ በሚገባ። የኢህአዴግ አመራሮችና ደጋፊዎች እኮ ሰዎች ናቸው። አሁን አገሪቱ ላይ ያለው አደጋ ያሰጋቸዋል። ከሁሉም በላይ ሰላም ለነሱም ያስፈልጋቸዋል። ያለ ስጋት ተራ ሰው ሆነው መኖር የሚፈልጉ አሉ። የግፍና የጭቆና መጠን ሲያልፍ ህዝብ እንደሚነሳ ጠንቅቀው ያውቃሉ። የግፈኛ መሪዎች መጨረሻ ምን እንደሚመስል ይረዳሉ። ችግሩ ያለው እነሱና ደጋፊዎቻቸው ወደ እርቅ እንዲመጡ የሚኬድበት መስመር አግባብ ያለው መሆኑ ላይ ነው። የመተማመን ችግር አለ።
ጎልጉል፦ እርቅ የጀመሩና አሁንም እየሰሩ ያሉ አሉ?ዶ/ር ተጋ፦ ካሉ ጥሩ ነው። እኔ ግን የማወራው ሌሎች ስለጀመሩት እርቅ አይደለም። እኔ የምናገረው የእውነተኛው እርቅ መንገድ ለገባቸው፣ የእርቅ ሃሳብ ላላቸው፣ ያልተነካኩና ለእርቅ ተግባር ቢነሱ የህዝብ ይሁንታና አመኔታ ማግኘት ለሚችሉ፣ ኢህአዴግም አክብሮ ሊያነጋግራቸው ፈቃደኛ ይሆናል ብዬ ለማምንባቸው ክፍሎች ነው። እርቅ ጀመሩ የሚባሉትን እነዚህን ሰዎችም ሆኑ ክፍሎች አላውቃቸውም። የምናገረው ቢጀምሩት ይሳካላቸዋል ብዬ ለማምንባቸው ሰዎች ለህሊናቸው ነው። የአገራችን ጉዳይ ያገባናል ለሚሉ ጨዋ ስብዕና ላላቸው ወገኖች ነው። እንግዲህ ይህንን ስል ከሁሉም ወገን ኢህአዴግን ጨምሮ ነው። አሁን አገራችን ያለችበት አሳሳቢ ወቅት ጤና ለነሳቸው፣ የወደፊቱ ትውልድ እድልና እጣ ፈንታ ግራ ላጋባቸው የኢትዮጵያ ልጆች ነው።
ጎልጉል፦ እውነተኛ እርቅ ምንድ ነው?ዶ/ር ተጋ፦ ስለ አቀራረቡ መናገሩ የሚሻል ይመስለኛል። ከላይ የጠቀስኳቸው ክፍሎች ውስጥ አገራችንን ሊታደጉ የሚችሉ፣ የመጪውን ትውልድ መከራ ሊገፉ የሚችሉ ነገር ግን ዝምታን የመረጡ የተከበረ ስብእና ያላቸው ወገኖች አሉ። እነዚህ ዝምታን የመረጡ ወገኖች ዝምታን የመረጡበት በርካታ ምክንያቶች ይኖራቸዋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከውስጥም ሆነ ከውጪ ስድድብ ነው። አንዳንዴ ቃላት እንኳ አይመረጥም። ሰው በስድብ ፖለቲካና ባለመከባበር የሚደረገው አተካሮ የሰለቸው ይመስለኛል። አንግዲህ እንዲህ ያለው መንገድ አልመች ብሏቸው ዝም ያሉትን ከተሸሸጉበት እንዲነሳሱ ማድረግ የመጀመሪያው ስራ ነው። ሌላው እርቅ የምትጠይቀውን ክፍል ማክበር ነው። እየዘለፍክና እያዋረድክ እርቅ መጠየቅ በባህላችንም ቢሆን አያስኬድም። በመከባበር ልዩነትን ማሳየትና ተቃውሞን መግለጽ የሚቻልበት መንገድ ሲፈጠር አድማጭ ማግኘት ይቻላል። በዚህ መልኩ መነጋገር ይጀመራል። እውነተኛ እርቅ የሚጀመረው የእርቁ አጀማመር ክብር የተሞላበት ሲሆን ነው። ሲጀመር መከባበርና የህዝብን ይሁንታ ማግኘት ከተቻለ የቀረው ጉዳይ ሂደት ነው የሚሆነው። ራሳቸውን ያከበሩና የጸዳ ማንነት ያላቸው ወገኖች ከየትኛውም ወገን ድጋፍ አላቸው። ከበሬታም አይነፈጉም። ኢህአዴግ ራሱም ቢሆን ሊገፋቸው አይችልም። አላማቸውና መሰረታቸው እርቅ ማውረድ መሆኑ ከተረጋገጠ ሊገፉ ወይም እምቢ ሊባሉ የሚችሉበት መንገድ የለም። ሁሉም ነገር የሚመነጨው ከስብዕናቸው ነውና ስብዕናቸው ያማረ ሰዎች ተሰባስበው እርቅ ላይ ቢሰሩ የሁሉም ስጋት ተቀረፈ ማለት ነው። ሌላ ትርጉም ካልተሰተው በቀር እርቅ አሁን ላለችው ኢትዮጵያ ፈውሷ ነው።
ጎልጉል፦ የሐይማኖት መሪዎች ሚና ምን ሊሆን ይችላል?ዶ/ር ተጋ፦ የሐይማኖት መሪዎች ነው ያልከው? እንደው ለመሆኑ እዛ ደረጃ የደረሱ አሉ? ካሉ ጥሩ ነው። እኔ ግን እስካሁን አላየሁም። የራሳቸው የግል አመለካከት ቢኖራቸውም ለጊዜው እሱን ወደ ጎን አድርገው ለእርቅ ቢሰሩ ደግ ነው። ግን …
ጎልጉል፦ ቄስ ገመቺስና ቄስ ኢተፋ ጎበና የጀመሩት እርቅ ነበር፤ዶ/ር ተጋ፦ ለትግል መንስዔ የሆኑ ሰዎች የእርቅ አፋላላጊ መሆን የሚችሉ አይመስለኝም። ከጅምሩ የህዝብን ይሁንታ ማግኘትና አለመነካካት ያልኩት እዚህ ጋር ይመጣል። ከቤተክርስቲያን ሃላፊነት በላይ በእርቅና በሰላም ፍልስፍና ማመን ይቀድማል። ራሳቸውን ለሰላምና ለእርቅ ፍልስፍና ያስገዙ ሰዎች የእርቅን ሂደትና የሚያስከፍለውን ዋጋ ስለሚረዱ እንዲህ አይነት ሰዎች ቢሆኑ ይመረጣሉ ባይ ነኝ። አሁን የጠቀስካቸው ወገኖች የጀመሩት ስራ ድጋፍ የሚያሻው ደረጃ ከደረሰም ማገዝ ነው።
ጎልጉል፦ በአንድነት ያምናሉ?ዶ/ር ተጋ፦ አንድነት የተሰጠን ነው። እምነት ነው። በፍጹም ሊፋቅ አይችልም። አንድነት ውስጥ ልዩነት፣ በልዩነት ውስጥ ደግሞ አንድነት አለ። የምናምረው በልዩነታችን ነው። በልዩነታችን ውስጥ የሚፈጠረው አንድነት ደግሞ ያደምቀናል። ልዩነት በየጊዜው የሚያድግ፣ ወደፊትና ወደኋላ የሚለጠጥ የላስቲክ ይዘት ያለው ነው። ስለዚህ ይህንን እንደ ላስቲክ የሚለጠጥ ልዩነት ስንይዘው፣ “ያንተ ማንነት እኔን አይረብሸኝም” የሚለው እሳቤ ውስጥ ሁልጊዜም መኖር እንችላለን። ያንተ ቋንቋ፣ ማንነት፣ አስተሳሰብ፣ አያስፈልገኝም የሚል ጉዳይ ከተነሳ የላስቲክ ይዘት ያለውን ልዩነት ባህሪውን ወደሚሰበርና የሚቀነጠስ ቁስ ይቀይረዋል። እንዲህ ያለው እርምጃ አደጋ አለው። እኔ እንግዲህ እንዲህ ያለውን አስተሳሰብ ከሚቃወሙ የአንድነት አማኞች ውስጥ ነኝ …
ጎልጉል፦ ስለ እርቅ እንመለስና የውጪ ሃይሎች /መንግስታት/ ካልገቡበት አይሆንም የሚሉ አሉ፤ በተለይም ተጽዕኖ ፈጣሪ አገሮች፤ዶ/ር ተጋ፦ እስከማውቀው ሕዝብ እውቅና የሰጠው እርቅ ስለመከናወኑ አልተሰማም። እኔ በግል ህዝብ እውቅና የሰጠው እርቅ ስለመኖሩ መረጃ የለኝም። በመጀመሪያ እርቅ በጓዳ ሲሆን ክብር የለውም። እርቅ በግልጽና ባደባባይ መሆን አለበት። ከላይ የገለጽኳቸው ወገኖች ከተሸፈኑበት መጋረጃ ከወጡና ለእርቅ ከሰሩ ብዙ ርምጃ መራመድ ይቻላል። የውጪ ሃይሎችን ማካተት ተገቢ የሚሆንበት አግባብ ብዙ ነው። እንደውም በገሃድ እርቁ ሲጀመር ለእርቁ ስራ የሚተባበሩ አገራትም አብረው መገለጽ አለባቸው። ለምሳሌ በኤርትራ ጉዳይ ላይ ኖርዌይ ብዙ ሚና ተጫውታለች። በወቅቱ ሚናዋ ደስተኛ ባልሆንም አስፈላጊ የሆኑ አገሮች እንዲካተቱ ማድረግ ተገቢ ይመስለኛል።
ጎልጉል፦ በተደጋጋሚ ዝምታን የመረጡ እንዲነሱ ይጠይቃሉ። በውል ስም ጠርተው ለዚህ ተግባር ተነሱ የሚሏቸው ወገኖች ካሉ?ዶ/ር ተጋ፦ ብዙ ታሪክ መለወጥ የሚችሉ ወገኖች አሉ። ራሳቸውን ከአገራቸው ፖለቲካ አግልለው የመነኑ አሉ። ራሳቸውን የፖለቲካ ባህታዊ ያደረጉ አሉ። እነዚህ ባህታዊ ፖለቲከኞች እንዴት እንዲቀሳቀሱ ማድረግ እንደሚቻል ያሳስበኛል። ብዙ እርቅ ላይ መስራት የሚችሉ ወገኖች አሉ። እነዚህም ወገኖች ከሸፈቱበት የ”አያገባኝም” መንገድ ተመልሰው ማየት እፈልጋለሁ። ስለዚህ ድንገት ቢሰሙኝ ብዬ ነው ደጋግሜ የጠቀስኳቸው።
ጎልጉል፦ ፖለቲከኛ ነበሩ? አሁንስ?ዶ/ር ተጋ፦ ፖለቲከኛ አይደለሁም። አጥብቄ የምጠየፈው ነገር ነው። አንዴ እዚህ፣ አንዴ እዚያ የመርገጥ ባህሪ የለኝም። የመገለባበጥ ነገር አይገባኝም። አቋራጭ ብሎ ነገር አላውቅም።
ጎልጉል፦ ግን በቂ ልምድ ያለዎት ይመስላል፤ዶ/ር ተጋ፦ (ሳቅ ብለው) … ልምድ!! ስለ አገራችን ፖለቲካ አንድ ነገር ልበል። የእኛ ህዝብ ቦይ ነው። መንገድ ካሳየኸው ዝም ብሎ ይጎርፋል። አሁን ታዲያ ቦዩ በዛ። ቦዮቹ ደግሞ ትንንሽ ሆኑ። ትንንሽ ስም ያላቸው ሆኑና እንደ ስማቸው ትንሽ፣ ትንሽ ሰዎችን ይዘው ቀሩ። እነዚህ ትንንሽ ቦዮች የጥቂት ብልጣብልጦች መጠቀሚያ ሆኑ። ባህሪያቸውና ተፈጥሯቸው ትንሽ በመሆኑ ጥቂቶች አትራፊ ሆኑና አብዛኞች ከሰሩ። ይህ አካሄድ ያላስደሰታቸው አብዛኞች ራሳቸውን አቀቡ። አድፋጮች በዙና /silent majority/ ተባሉ። ከስማቸው እንደምንረዳው እነሱ ይበዛሉ። አሁን ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት እነዚህ ዝምተኛ፣ ባህታዊ ፖለቲከኞች፣ የመነኑ ዜጎች ተመልሰው ለእርቅና ለሰላም እንዲሰሩ ማሳሰብ የሁሉም ቀና ዜጋ ተግባር ሊሆን ይገባል። እኔ እንግዲህ እንደዚህ አስባለሁ። የተደበቁ ተመራማሪዎች አሉ። ሌሎች አገራትን የሚጠቅሙ ክቡር ዜጎች አሉን። አገራቸውን የሚወዱ ህዝብን የሚፈሩ አሉ። ከሁሉም በላይ ለህሊናቸው የሚኖሩ ዜጎች አሉ። ኢትዮጵያ የልጆች ደሃ አይደለችም። እነዚህ ዜጎች ለህዝብ ሲሉ፣ አገራቸው ሰላምና እርቅ እንዲወርድላት ሲሉ ከተደበቁበት ሊወጡ ይገባል።
ጎልጉል፦ ከህወሃት ሰዎች ጋር ይተዋወቃሉ?ዶ/ር ተጋ፦ የቀድሞውን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ስዩም መስፍንን አውቃቸዋለሁ፤ አብረን ተምረናል። ባለስልጣን ከሆኑ በኋላ ተገናኝተንም ነበር። በግል በእርቅ ዙሪያ ላነጋግራቸው እችላለሁ። ሌሎችም ሰዎች አሉ። ኢህአዴግ ውስጥ ቀና ሰዎች እንዳሉ መታመን አለበት። ቀና የትግራይ ልጆች አሉ። የወደፊቱ ችግር የሚያሳስባቸው ጥቂት አይደሉም። ደጋግሜ እንደነገርኩህ ዋስትና የሚናፍቁ ባለስልጣኖች ብዙ ናቸው። ሰላም የሚመኙ ብዙ ናቸው። መንገዳቸውን መመርመር የሚፈልጉ ጥቂት አይደሉም። ግን በስድብና በጥላቻ ሊሆን አይችልም። በመከባበር የሚመሰረት መቀራረብ ወደ አንድ የእርቅ ሃሳብ ያመጣል። ጊዜ ቢወስድም መጀመር አለበት። ሲጀመር ግን በክብር መሆን አለበት። ህዝብም እውቅና የሚሰጠው ሊሆን ይገባል።
ጎልጉል፦ እርስዎ የሚያምኑበት እርቅ በዋናነት ምን መያዝ አለበት?ዶ/ር ተጋ፦ እርቅና ሰላም ከፍትህ ጋር። ፍትህ የሌለበት እርቅ ዋጋ የለውም። ሰላምም አያመጣም። ግብጽ ጥሩ ምሳሌ ናት። አሁን የተነሳውን የፕሬዚዳንት ሙርሲን ደጋፊ ምን ታደርገዋለህ። ፍትህ ካላገኘ ለመሞት ተነስቷል። በሌላ በኩል ሙርሲን አውርደው የተቀመጡ አሉ። ለሙርሲ ደጋፊዎች ምላሽ ቢሰጥ አውርደው የተቀመጡትና የፈለጉትን ለመምረጥ ጊዜ ገደብ የተቀመጠላቸው ይነሳሉ። ሲጀመር ፍትህና እርቅ ተጣምረው ባለመከናወናቸው ችግሩ እየተባበሰ ሄደ። ስውር ጉዳዮች እንዳሉ ሆነው ማለቴ ነው። ስለዚህ እርቅና ፍትህ የሚለያዩ ነገሮች አይደሉም። ፍትህ ያለበት እርቅ እንዲሰፍን ተግተን መስራት አለብን። አገራችን ያለችበት ሁኔታ ቸል የሚባልበት አይደለም። በኋላ ሁላችንንም ይቆጨናል። እርቅ ላይ ትኩረት ማድረግ ግድ ነው። የፖለቲካ ለውጥ እንኳን ቢኖር የተዘራውን ክፉ ዘር ለማክሰም እርቅ ግድ ነው።
 

Friday, August 23, 2013

የወጣቱ የመጥለፍ ፖለቲካ በ” ይልቃል አዲሱ ልደቱ…? ” ፀሁፉ ውስጥ

በጥያቄ ምልክትና እና በቃለ አጋኖ የታጀበውን ‘’ይልቃል አዲሱ ልደቱ” በሚል ርዕስ ወጣት ዳዊት ስለሞን በብዕር ስም /አይናለም/ የተፃፈውን ባለ ብዙ ሀሳብ ፅሁፍ አነበብኩት ፡፡ አንድ ፅሁፍ ሲፃፍ አንባቢ ሊታዘብ ይችላል ሰለዚህ እውነት ላይ እና እየታዩ ካሉ ነባራዊ ሁኔታዎች አንፃር መቃኘት አለበት የሚለው ዋና ጉዳይ በዚህ ፀሁፍ ውስጥ ለኔ አልታየኝም ፡፡ በፅሁፉ ውስጥ አንባቢን ለማሳመን የተደረጉ ውጣ ውረዶች ከመጥቀሴ በፊት ፀሀፊው አባል በሆነበት አንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ውስጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተመለከትኩትን የሚበረታታ ጉዳይ ከማሳሰቢያው እጠቅሳለሁ፡፡
ማሳሰቢያ ‘’ይልቃል አዲሱ ልደቱ” ፅሁፍ ፀሀፊ ዳዊት ሰለሞን የአንድነት ፓርቲ ልሳን የሆነው ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ኣዘጋጅ ለመሆኑ አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የአንድነት አባል ስለነገረኝ ከዚህ በታች የምጠቀመው የብእር ስሙን ሳይሆን ዳዊት የሚለውን ዋና ስሙን መሆኑን አሳውቃለሁ፡፡
መኢአድ ሲባል ኢ/ር ሀይሉ ሻወል፣ ደቡብ ህብረት ሲባል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ፣ ኦብኮ ሲጠቀስ ዶ/ር መረራ ጉዲና… የፖለቲካ ተክለ ሰውነት ለብሰው ብቅ ይሉብናል፡፡ ይህ የፖለቲካ ተክለ ሰውነት በአንድት ውስጥም ግዝፈቱን ሳይቀንስ ተንሰራፍቶበት ቆይቷል፡፡ ይህ ማለትም አንድነት ሲባል በየደቂቃው የሚለዋወጥ አቋም ያለው ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው እና ባለመልካም ባህሪው ዶ/ር ሀይሉ አርአያ ድቅን ይሉብን ነበር እነአቶ አስራት ጣሴን አስከትለው፡፡ ወጣት ዳዊትም በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ የሚታዩ ችግሮች ብለው ከጠቀሱዋቸው መካከል የግለሰብ ተክለ ሰውነት መገንባት አንዱ ነው፡፡
እኔም የግለሰብን ተክለ ሰውነት አንዱ መስፈርት አድርጌ ፓርቲዎችን ስገመግም አንድነት አሁን ካሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ውስጥ የተሻለ ነው እንድል ያደረገኝ ከግለሰብ ትከሻ ላይ ወርዶ አበረታች የሚባል የቡድን ስራ ማክናውን ላይ በመሆኑ ነው፡፡
የተመለከትኩትን ጠንካራ ጎን ከገለፅኩ በኋላ የፓርቲው አባል የሆኑት ወጣት ዳዊት ፅሁፍ ላይ ላተኩር፡፡ ሀሳብን በነፃነት ለመግለፅ ያደረገውን ጥረት በማድነቅ ፅሁፉ መጀመሪያ ላይ የጠቀሱት የደርግ/ የኢህአፓ /የመኢሶን ፖለቲካዊ መጠላለፍ ዛሬ ላይ እንዲመጣ ወይም ዛሬ ላይ ያለው የመፈራረጅ ፖለቲካ እንዲቀጥል ታጥቀው የተነሱ ነው የሚመስለው፡፡ እንዴት! ማለት ጥሩ….. በአዲስ መስመር ከመቀጠሌ በፊት እኔ የሰማያዊ ፖርቲ አባልም ደጋፊም አለመሆኔ ሊታወቅ ይገባል፡፡
አንባቢን ለማሳመን እና ሰማያዊ ፓርቲ የወጣቶች ስብስብ መሆኑን ለማጣጣል የአቶ ልደቱ ወጣት መሆን በመጥቀሥ በጥሩ ሁኔታ እየተቀሰቀሰ ያለውን ፖለቲካ ለመጥለፍ ‹‹አዲሶቹ ጎጆ ወጪዎች ከመጀመሪያው ቤታቸው ሲወጡ በአብዛኛው ባዶ እጃቸውን አይሆኑም፣የእናት ፓርቲያቸውን የፖለቲካ ፕሮግራም፣አደረጃጀትና አባል ይዘው ሹልክ ይላሉ፡፡ለዚህ እንደምሳሌ ኢዴፓና ሰማያዊ ፓርቲን መውሰድ ይቻላል፡፡›› ይሞክራሉ፡፡ እኔም አንድ የመጥለፉ መንገድ ልከተልና ፀሀፊውን ልጠይቀው፡፡ ቅንጅት የአራት ፓርቲዎች ጥምረት ነው፡፡ መሪዎቹ ታስረው ሲፈቱ በጋራ መቆም አቃታቸውና የየራሳቸውን ደጋፊና አባል በመያዝ ለአራት ተሰነጣጠቁ፡፡ከግንቦት 7 በስተቀር ሁሉም የሰላማዊ ትግል መርጦ የቅንጅቱን መንፈስና ፕሮግራም ለማስቀጠል በያለበት ይንቀሳቀሳል፡፡ ከነዚህ ውስጥም አንድነት አንዱ በመሆኑ የእናት ድርጀቱን አባል ፕሮግራም ይዞ ሹልክ አለ ማለት ነው ወይስ አንድነት የተለየ ፕሮግራም አረቀቀ? ይህን ለመመለስ የቅንጅትንም የአንድነት በደንብ ፕሮግራሞች ማየት ያስፈልጋል እንዳትረሳው!
የሰማዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር ላይ ያስቀመጠው ቅሬታ / ግን ሰይጣናዊ ቅናት ብለው በትክክል ይገልፀዋል/ ጠቅለል አርጌ ለመግለፀ በሁለት መክፈል እፈልጋለሁ፡፡ ሊቀመንበሩ ላይ የቀረበው ቅሬታ ለፖለቲካው በማሰብ በሚል እና ፀሀፊው ጎልቶ ለመውጣት ባለው ጉጉት የሚከተላቸው መንገዶች በሚሉ ፡፡
ለፖለቲካው በማሰብ
ኢ/ር ይልቃል /የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር/ “ፓርቲዎች አሉ ብለን አናምንም ተባበሩ የምትለን ከማን ጋር ነው ? መድረክ ምን ሰራ አንድነትና መድረክ እየተባሉ አይደለም? አንድነት ውስጥ የገባው ብርሃን ወጥቷል እኛ ከማን ጋር እንተባበር ? ብለዋል ብሎ ወጣት ዳዊት ይኮንናል፡፡ የኢ/ር ይልቃል ንግግር ላይ ያለውን ስህተት ለማሳየት ፓርቲዎቹ የሰሩትን ምንም መረጃ ማቅረብ ስላልቻለ በደፈናው በህብረት ለመስራት አንፈልግም ብለዋል ሲል ተንከባሎ ያልፋል፡፡ የመድረክ አባል ፓርቲዎች የደቡብ ህብረት ከፕ/ር በየነ ሳምሶናት ውስጥ መውጣት ሳይችል፣ ኦፍዴን ከአቶ ቡልቻ የግል ንብረትነት ሳያልፍ፣ ኦብኮ ከዶ/ር መራራ የኮሜዲ ምሽት ሳይላቀቅ ፣አረና አባላቱ በነፃ ዝውውር ለሰማያዊ ፓርቲ እየፈረሙ ባሉበት ሰአት እና አንድነት በኣዛውንቶችና በወጣቶች መሀክል በሚደረግ ገመድ ጉተታ ፖለቲካ ውስጥ ነው ያለው ስለዚህ ከማን ጋር በህብረት ይስራ ነው የሚባለው፡፡ በተጨማሪም ብርሀንም ከአንድነት የወጣው ገመድ የጉተታ ውጤት ይዞት የሚመጣው ጦስ አስግቶት ነው፡፡ ታዛቢ ስላለ እውነቱ ይህ መሆኑን መግለፅ ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ የተቀረበው ቅሬታ ለፖለቲካው በማሰብ አደለም ለማለት እደፍራለሁ፡፡
በተጨማሪም አንድነትን ጨምሮ ሁሉም የመድረክ ፓርቲዎች ጥርት ያለ የፖለቲካ ፕሮግራም ስለሌላቸው መስማማት አልቻሉም ፡፡ ይህንን ስል በስሜት አለመሆኑን ለማስገንዘብ ሁለት ምሳሌ ልጥቀስ፡፡ የመሬት ጥያቄና የመገንጠል መብት ፓርቲዎቹ ከግንባርነት እንዳያልፉ ማነቆ ሆነው ስራ እዳይሰሩ ያደረጋቸውን ብቻ ማንሳት በቂ ነው፡፡ ይህም እውነት ሲገለጽ በሰማያዊ ፓርቲ ፕሮግራም ላይ የተቀረበው ቅሬታ ለፖለቲካው በማሰብ አይደለም ለማለት እገደዳለሁ፡፡
ጎልቶ ለመውጣት የሚደረግ ጥረት
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንድነት ከላይ እንደጠቀስኩት ከግለሰብ ስብእና ራሱን በማፅዳት የቡድን ስራን በመጀመር የሚያበረታታ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ ይህም የቡድን እንቅስቃሴ ባለፉት ግዚያት እንደተመለከትነው በተለያዩ የክልል ከተሞች በመንቀሳቀስ የቀዘቀዘው የህዝብ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ዳግም እንዲያንሰራራ ሚዛን የሚደፋ አስተዋፆ አድረጓል፡፡ ለዚህም አበረታች ጅማሮ ከፊትም ከኋላም በመሆን ከፍተኛ አስተዎ ያደጉትን ግርማ ፣ዳንኤል እና በላይን የመሰሉ ወጣት ፖለቲከኞችን ማመስገን ያስፈልጋል፡፡ በዛውም ልክ ይልቃል ጎልቶ ለመውጣት ይፈልጋል ተብሎ እንደተከሰሰው በአንድነት ህዝባዊ ንቅናቄም ውስጥም በበርካታ ወጣቶች ላይ ጎልቶ የመታየት ፍላጎት ሲከሰት ከርሟል፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዱ ወጣት ዳዊት ይግኝበታል፡፡ እንዴት የሚል ጥያቄ ከተነሳም መልሱን ክዚህ በፊት ወጣቱ የሚያድጋቸውን ጎልቶ ለመውጣት የሚደረግ ድርጊቶች ላሳይ፡፡ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አንድነት ፓርቲ ውስጥ የተመለከታቸውን ህፀፆች እንደጋዜጠኝነቱ እንዲታረሙ በበሳል ብእሩ ሲጠቁም የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የጋዜጠኛውን ጥቆማ በመቀበል የታዩትን ችግሮች ለማረም ደፋ ቀና ብለዋል፡፡ ነገር ግን ፍየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ የተባለው ብሂል በወጣቱ ዳዊት ላይ ተተግብሮ ‹‹ ተመስገን ደሳለኝ ሲያዳልጠው›› በሚል ጽኁፍ በአደባባይ ፓርቲውን ለምን ነካ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ በማለት እፍኝ እውቅና ለማግኘት ሲታገል መድከሙ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡ ይህ ተግባር በተመስገን ላይ ብቻ የተገደበ እይደለም ፡፡ ብዙ መጥቀስ ይቻላል ነገር ግን ዝም በመባሉ ያሸነፈ ስለመሰለው በተመሣሳይ ላሞኛችሁ አይናችሁን ጨፍሁ ብሎ በኢ/ር ይልቃል ላይ እንዲህ ሲዘምት ጎልቶ ለመውጣት በሚደረግ ጥረት የሚቀዘቅዘው የወጣቶች የፖለቲካ ተሳትፎ ስላሳሰበኝ ነው ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ የተገደድኩት፡፡
በአጠቃለይ የወጣቱ ፅሁፍ ለሀገራችን ፖለቲካ በማሰብ የቀረበ ሀሳብ ሳይሆን ጎልቶ ለመውጣት የሚደረግ ጥረት በመሆኑ የተጀመረው የህዝብን የማንቃት ስራ አዳክሞ ሀገሪቱን በአንባገነንነት ለሚመራው ኢህአዴግ ነው የሚጠቅመው፡፡ ስለዚህ ወጣት ዳዊት ገና ብቅ ብቅ የሚሉ ወጣት ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኛ ተመስገን ላይ በመፃፍ እውቅናን ለማግኘት ከመጣር ከላይ በአንድነት ውስጥ ከባድ እንቅስቃሴ እያደረጉ ያሉትን ምሳሌ በማድረግ ስራቸውን ማጉላት ላይ ብታተኩሩ ወይንም እነሱ ልምድ ካላቸው ፖለቲከኞች ጀርባ ሆነው ልምድ ቀስመው ዛሬ ለሀላፊነት የበቁበትን መንገድ መከተል በሳልነት መሆኑን ሳልጠቁም አላልፍም፡፡ በመጨረሻም ሰማያዊ ፓርቲ አዲስ መስመር…
ምስረታ ጀምሮ አወዛጋቢ የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ 8 አመት ሙሉ የቀዘቀዘውን የሀገሪቱ ፖለቲካ ሚዛን በሚደፋ መልኩ ለማሞቅ ( ለማንቀሳቀስ) ጥረት እያደረገ ነው፡፡ ነገር ግን የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም እና በፓርቲው ውስጥ ያሉት አመራሮች ከሊቀ መንበር ውጪ ያላቸው የፖለቲካ ብስለት በሰፊው ለህዝብ ስላላደረሰ አውዛጋቢነቱ እንዲቀጥል አድርጎታል ፡፡ ይህም የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም እንዲሁም በፓርቲው ውስጥ ያሉት ወጣት አመራሮች ያላቸው የፖለቲካ ብስለት ለሰፊው ህዝብ ካልደረሰ በሀገራችን ለዘመናት ለቆየው የመጠለፍ ፖለቲካ ጭዳ ይሆናል ባይ ነኝ፡፡ በተጨማሪም እንታገልለታለን ለምትሉት ህዝብ የማሳወቅ ፓርቲው ግዴታም አለበት፡፡

በአንዋር መስጂድ ፖሊስ ሙስሊም ሴቶች ላይ ከፍተኛ ድብደባ ፈጸመ! ጁምአ

August 23, 2013
 
ድምፃችን ይሰማ
ጭንቅላታቸው የተፈነከተና ደም ይፈሳቸው የነበሩ ሴቶች ታይተዋል!
ጥቂት የማይባሉ እናቶችና እህቶች ሰላታቸውን ሳይሰግዱ ወደ ቤታቸው ለመመለስ ተገደዋል!
ዛሬ የጅምአን ሰላት ለመስገድ በተገኙ እናቶች ላይ ፖሊስ ድብደባ መፈጸሙ ታወቀ፡፡ በመርካቶ አንዋር መስጂድ የዛሬውን የጁምአ ሰላት ለመፈጸም የተገኙ በርካታ እናቶችና እህቶች በፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድብደባ ተፈጸመባቸው፡፡ እነዚሁ ለጸሎት የተሰባሰቡ እናቶች ድብደባ የተፈጸመባቸው ከመስጂዱ ግቢ ውጪ አንጥፋችሁ መስገድ አትችሉም በሚል ነው፡፡ Ethiopian Musilms
ታላቁ አንዋር መስጂድና ሌሎችም መስጂዶች በጁምአ እለት የሚመጣውን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ማስተናገድ ስለሚሳናቸውና ስለሚሞሉ ህብረተሰቡ ውጪ አንጥፎ መስገዱ ባለፉት 15 ዓመታት የተለመደና የሚታወቅ ሀቅ ቢሆንም በሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ ብሄራዊ ጭቆናን እያሰፈነ ያለው መንግስት ሙስሊሞችን በሁሉም አቅጣጫ ለማጥቃት በማለም የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር በተለይም ሴቶች ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ቀጥሎበታል፡፡
በዛሬው ድብደባ ጭንቅላታቸው የተፈነከተና ደም ይፈሳቸው የነበሩ ሴቶች እንደነበሩ የታወቀ ሲሆን ጥቂት የማይባሉ እናቶችና እህቶች ሰላታቸውን ሳይሰግዱ ወደ ቤታቸው ለመመለስ ተገደዋል፡፡ መንግስት የሃይማኖት አክራሪነትን እታገላለሁ በሚል ስም በሙስሊሙ ላይ ብሔራዊ ጭቆና በማስፈን ላይ ይገኛል፡፡ የዚህ ጭቆና ዒላዎችም ልክ ዛሬ እንደታየው አረጋውያን እናቶችና እህቶች ሆነዋል፡፡
የእምነት ነጻነትን አክብሪያለሁ እያለ ደጋግሞ በሚዲያ የሚናገረው መንግስት በሕገ መንግስቱ የተቀመጡትን የእምነት ነጻነት መብቶች በመጣስ ሙስሊሙ ላይ ከፍተኛ በደል በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡ ሙስሊሙ ህብረተሰብ የራሱ የእምት ተቋም እንዳይኖረው ከማድረግ አንስቶ አዲስ እምነት በሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ በኃይል መጫን፣ የሙስሊሙን ማህበረሰብ መሪዎች ማሰርና ማሰቃየት፣ የመብት ጥያቄ ያነሱ ሰላማዊና ያልታጠቁ ዜጎችን መግደል፣ መስጂዶችን ማሸግ፣ ኢማሞችን ያለ ሕዝቡ ፍላጎት ከስራቸው ማፈናቀልና በራሱ ፍላጎት መንግስታዊ ኢማሞችን መተካት እና ሌሎችም በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሊፈጸሙ የማይችሉ ተግባራትን መንግስት ያለ ምንም ሀፍረት ሲፈጽም ቆይቷል፡፡
አሁን ደግሞ በክልሎች ሲካሄድ እንደነበረው ሁሉ ሙስሊሙን ሕብረተሰብ ከሰላት ለማቀብና ለማሸማቀቅ ለመስገድ ወደ መስጂድ የሄዱ ሙስሊሞችን ለጸሎት በተቀመጡበት ድብደባ ሲፈጸምባቸው እየተመለከትን ነው፡፡ የዚህ አይነቱ ተግባር በኢትዮጵያ ታሪክ ቢያንስ ባለፉት 90 ዓመታት እንኳ ያልታየ ድርጊት የእምነት ነጻነት በሕገ መንግስት ደረጃ በተደነገበት በዚህ ወቅት እየተፈጸመ መሆኑ ሙስሊሙ ህብረተሰብ የመንግስትን አላማና ግብ በአንክሮ አንዲያጤነው የሚጋብዝ ነው፡፡ ባለፈው ዓመት በደሴ ሸዋ በር መስጂድ መስጂድ የሞላባቸው የከተማው ሙስሊሞች ውጪ አንጥፋችሁ ሰግዳቹሀል በሚል ፖሊስ ከፍተኛ ጥቃት ሰንዝሮ በርካቶችን ለእስርና አሰቃቂ ድብዳባ መዳረጉ ይታወሳል፡፡
መንግስት መሰል ሁኔታዎችን ኹከት ለመፍጠር የሚጠቀምባቸው በመሆኑ ሁኔታዎችን በትእግስት ከማሳለፍ በዘለለ ድርጊቱ ሲፈጸም ፎቶ ግራፍና ቪዲዮ ማንሳት ሊዘነጋ የማይገባ ተግባር መሆኑን ማስታወስ ያሻል፡፡
አላሁ አክበር!

ECADF Ethiopian News

በአሜሪካ ግቢ ቦምብ እላያችን ላይ ሳይፈነዳብን ተገኘ

ምስጋና ለኢትዬጲያ ፌደራል ፖሊስ እና ለብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ኤጀንሲ ጥምር የጸረ ሽብር ቡድን ግብረ ሃይል
በአዲስ አበባ ከተማ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በተለምዶ በአሜሪካ ግቢ ራስ ስዩም ሆቴል አጠገብ ወደ አርባምንጭ ከተማ ጭነት የሚጫንበት ቦታ አካባቢ በሚገኘው ራህመት ኤጀንሲ በር ላይ ኮድ 3 የታርጋ ቁጥር 73189 በሆነ አንድ |የጭነት ማመላለሻ አይሱዙ ጎማ ስር የአጅ ቦምብ ተገኘ ተባለላቹ፡፡፤
ይህን የእጅ ቦምብ የአዲስ አበባ ከተማ መደበኛ ፖሊሶች ቀደም ብለው በእጃቸው ይዘውት እንደነበር የአይን እማኞች ገልጸዋል፡፤የእጅ ቦምቡን ጠዋት ይዘውት ከነበሩት ሁለት ፖሊሶች መካከል የአንዱ ፎቶ ከዚህ በታች ተያይዞ ቀርቧል|፡፡ሙስሊሙ የመረጃ ሰው ሆኗል፡፡አልሃምዱሊላህ
ይህ ቦምብ አፈንጂው እና ቦምባ አምካኞች ያደረጉት ትንቅንቅ አንድ ወንድም ያደረሰኝን መረጃ ላካፍላችሁ፡፡የተቀረውን መረጃ በቦታው ከነበሩ እና ከኢቲቪ ማጣራት ትችላላችሁ
አንድ ግለሰብ ቦምብ ይዞ በመምጣት አንድ የጭነት መኪና ጎማ ስር ቦምቡን አስቀምጦ ዞር ይላል፡፤ በመቀጠልም ይህ ግለሰብ ከቆይታዎች ቡሃላ ተመልሶ በመምጣት እዛው አካባቢ ይቆማል፡፡ በመቀጠልም ፖሊስ ይህን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ያውለዋል፡፡ከዛ ፖሊስ ይህን ግለሰብ ሲፈትሸው ሌላም ቦምቦች በኪሱ ስር ያገኛሉ፡፡ ከዛ የፌደራል ፖሊስ እና የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ኤጀንሲ የጸረ ሽብር ግብረሃይል ይህን አሸባሪ ግለሰብ በህዝብ እና በንብረት ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር አዋሉት፡፤ ከዛ የፈንጂ አምካኝ ግብረሃይል መጣና መኪናው ጎማ ስር የተቀመጠውን ቦምብ እንዳይፈነዳ በጥንቃቄ በማድረግ አክሸፈው፡፤ከዛ በቃ ድራማው በሚገርም ሁኔታ በመጠናቀቁ ቀረጻ ተካሂዶለታል፡፡በጥሞና ስላነበባችሁልኝ አመሰግናለው
ቆይ ትንሽ ልጨምርላችሁ ይህ አሸባሪ ግለሰብ እራሱ ያስቀመጠው ቦምብ ጋር በመምጣት መፍንዳት እና አለመፈንዳቱን የሚጠባበቀው ምንኛ አስገራሚ አሻባሪ ነው???? ቀጥሎም ለሌላ ተልኮ የሚሆን ቦምቦችን በኪሶ ሸክፎ ይዞ ነበር፡፤ይህንንም አደገኛ ሊፈጸም የነበረውን የሽብር ጥቃት በማስመለከት ለኢቲቪ ዜና የሚሆን ድራማ ይህ አሸባሪ ግለሰብ ከፌደራል ፖሊስ እና ከብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ኤጀንሲ የጸረ ሽብር ግብረ ሃይሉ ጋር በመሆን ሲከውን እንደነበር የአይን እማኞች ገልጸዋል፡፡ የዚህን ሙሉ ዜና ዝርዝር ማታ ኢቲቪ ዜና ላይ ይጠብቁ:;
ከዚህ ቀደም በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያም ተመሳሳይ ጠቀጣጣይ የሆኑ ሁለት ስሊንደሮች ተቀምጠው መገኘታቸው ኢቲቪ ዘግቦልን ነበር፡፡ደሞ ሌላ ቀን ምን አይነት ነገር መያዡን እንሰማ ይሆን???? ፡፡
ምናለ ኢትዬጲያ ሃገሬ ለአለም ሰላም ሁሌም በምታደርገው ጥረት የምትደነቅ በመሆኗ እንዲህ አይነት የፀረ ሽብር ግብረ ሃይሏን ችሎታ ለሌሎች ሃገሮችም ልምዷን ብታካፍል እና ቦምቦች ሳይፈነዱባቸው ሁሌም ከነአሸባሪው በቁጥጥር ስር እንዲ ያውሉ ብትረዳቸው ?????
እኔስ ምንም አልልም ግን ብቻ ይሄ ድራማ እንዲ እያጃጃለን አንድ ቀን የምር አፈንድተውት እንዳይጨርሱን እሰጋለው!!!
ለማንኛውም ቦንቦቹ ሳይፈነዱ በቁጥጥር ስር ስለዋሉ አልሃምዱሊላህ በዚህኛው ድራማ ሂወታችንን አልቀጠፉብንም፡፡
አላህ የኢትዬጲያን ህዝብ
 ለድራማ ተብሎ ከሚደረስ ጥቃት ይጠብቅልን!!!!
ድል ለኢትዬጲያ

Ethiopia: Device found at Addis Ababa’s international airport was not an explosive

  • Posted by Selamawit on August 23, 2013 at 12:19am
  • View Blog
  • By Tesfa-Alem Tekle
    August 22, 2013 (ADDIS ABABA) - A senior government official said on Thursday that a device found at Addis Ababa’s international airport was not an explosive, as was recently was reported by Sudan Tribune and other media outlets.
    “The device was not an explosive or type of bomb but just a flammable cylinder gas”, communication minister Shimels Kemal told Sudan Tribune, adding that a counter-terrorism team had been established to deal with the incident.
    Kemal said the situation is under investigation and no suspect has yet been arrested.
    Airport authorities today similarly confirmed that the devices found were gas cylinders.
    The two gas cylinders, which could potentially explode if they caught on fire, were first found by airport janitors.
    The two devices were found around the departure terminal of the country’s largest airport.
    Airport officials said details of the incident will be announced once the investigation is complete, declining to provide further comment on the matter.
    The investigation team is yet to determine if the devices were deliberately deposited at the airport in order to commit a terrorist attack.
    Addis Ababa Bole International Airport is one of the continent’s busiest airports, with a current traffic movement of nearly 2 million passengers per year, according to Ethiopian Airports Enterprise (EAE).
    EAE has finalised an expansion and upgrade project at the airport which would enable it to park more passenger jets at a time.
    The airport has been serving to the East African nation as an international gate way for over 40 years.

    Top UDJP Official Nebiyou Bazezew in critical condition after assault

    August 22, 2013
    The Horn Times Newsletter August 22, 2013
    by Getahune Berkeley-South Africa

    Drunk with ethnocentric tyra
    UDJP tour bus mobbed by its diehard supporters in Fiche. (Pic minilik Salsawi)
    UDJP tour bus mobbed by its diehard supporters in Fiche. (Pic minilik Salsawi)
    nny, the Ethiopian ruling minority junta under the leadership of Prime Minister Hailemariam Desalegn is continuing its crack down on opposition groups with devastating cruelty and mercilessness.
    Currently, the inept and abusive regime and its cadres are focusing on the opposition party UDJP’s nationwide campaign for change under the banner of “millions of voices for change.”
    According to Finotenetsanet weekly Amharic tabloid, as part of the naked assault on freedom of association, UDJP Addis Ababa zone executive committee member Nebiyou Bazezew Wubalem, 42, and colleague Messay Teke were severely assaulted and robbed by more than sixteen TPLF cadres in the town of Fiche; about 45 km north of the capital while on campaign to mobilize the local youth for Saturday 25 August 2013 peaceful march.
    The incident took place yesterday 21 August 2013 at 9pm local time.
    The injured duo have arrived in Addis Ababa this morning, 22 August for further medical attention and UDJP acted swiftly and decisively by sending another strong team to the town of Fiche.
    The town’s deputy security chief, Haileeyesus Beyene, spearheaded yesterday’s well-coordinated attack and robbery on UDJP members.
    “Nebioyu Bazezew Woubalem became a target before even going to the town of Fiche after his recent interview with you guys (the free media in exile). I spoke to him today at 12 o’clock and despite the ordeal he is in good spirit and raring to go. His injuries are not life threatening but he was in critical condition earlier. We all hope and pray that he will be back to work soon.” A close friend of the brutally mauled UDJP stalwart Ato Nebiyou Bazezew who requested anonymity told the Horn Times from Addis Ababa.
    infohorntimes@gmail.com

    የልማታዊ ጋዜጠኞች አንዝህላልነት እና የአብርሃ ደስታ እማኝነት “የኢትዮዽያውያን ህይወት በዓረብ ሀገሮች “

    Friday, August 23, 2013
    ከነብዩ ሲራክ
    ባሳለፍነው ሳምንት በሳውዲ አረቢያ ግፍ ተፈጸሞባቸው ወደ ባገር ቤት የሚሸኙ እህቶች የመኖራቸው መረጃ ደረሰኝ ። በተለይም በቅርብ እከታተላቸው የነበሩ አህቶች እንግልት በመጠቆም በዚው በፊስ ቡክ የማለዳ ወግ ዳሰሳየ ላይ አንድ መልዕክት አስላልፊ ነበር! መልዕክቱም ለልማታዊ የሃገር ቤት ጋዜጠኞች ሲሆን የመልዕክቱ ፍሬ ሃሳብ ” የምንናገረውን ማመን መቀበል አቅቷችሁ እንደ ጠላት ከምታዩን ረቡዕ ወደ ቦሌ አየር ማረፊያ ሂዱና ከፍተኛ ግፍ ተፈጸደሞባቸው ከሳውዲ ተጠርፈው ወደ ባገር የሚገቡትን የኮንትራት ሰራተኞችን ተመልክቱ !”የሚል ነበር።
    ንቁ እዝነ ልቦንና ያልታደሉት ልማታዊ ጋዜጠኞች በቦታው ሄደው ከቤሩት የተመለሱትን ሻንጣ የደረደሩ እህቶች በቴሌቪዥኑ መስኮት ብልጭ አድርገው ከማጥፋታቸው ባለፈ ከሳውዲ ያለጫማና የረባ ልብስ ተደብድበውና ተደፍረው የተመለሱትን ግፉአን ሊያሳዩን እንኳ አልፈቀዱም! ጋዜጠኞቻችን አልተሳሳቱም!!! የተሳሳትኩት እኔ ነኝ!!! ያን ሰሞን “ስደት ይቅር ” ምንቴስ ሰፊ ሽፋን በየሚዲያው እየሰጡ ፣ የደበቁትን መከራችን እያሳዩ እያሉ ህዝበ አዳም ፣ ሃገሬውን ሲያስለቅሱን የከረሙት ወደ ነፍሳቸው ተመልሰዋል ብየ በማሰቤ ስህተቱ የእኔ ግምት ነው!!! ጉዳታችን እዩት ቀሪው እንዲማርበት ፣ ሃላፊዎቻችን ይዩትና ወደ ዘነጉት የዜጎች ጉዳይ ያተኩሩ ዘንድ የተገፊ ግፉአኑን ጉዳይ ተከታትየ መጠቆሜ በአደባባይ ቃል የገቡትን ይፈጽማሉ ብየ በማሰቤ የተሳሳትኩት እኔ ነኝ!!! ስህተቴ አንድና አንድ ነው!!! የአረብ ሃገሩን የስደት መከራ የሚፈልጉት ለፕሮፖጋንዳ እንጅ ቀሪውን ማስተማርን እንደልሆነ አለማሰቤ ነው ስህተቴ ! በእንዝህላል ልማታዊ ጋዜጠኞቻችን አዝኘም ብቻ ሳይሆን አፍሬ ዝም ማለቴ ግን እውነት ነው! ዛሬ ማለዳ ግን መልካም መረጃም የሚየ ስፈነጥዝ ባይሆንም መረጃው በመሰራጨቱ የተደሰትኩበትን መጣጥፍ ተመለከትኩ ።
    ሮብ ነሓሴ 15, 2005 ዓም ከአረብ ሃገር ወደ ሃገር የገቡትን እህቶች አብርሃ ደስታ አግኝቷ እንዳነጋገራቸው በማህበራዊ ድህረ ገጽ ካስተላለፈው መልዕክት ለመረዳት በመቻሌ ደስ አለኝ ! በገዥው የኢህአዴግ መንግስት አስተዳደር ላይ በተለይም ስለ ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ከመቀሌ ሆኖ በሚያሰራጫቸው የሰሉ ሚዛናዊ ሂሶች ተወዳጅነትን እያተረፈ የመጣው አብርሃ ድስታ ግፉአን እህቶቸችን ቦሌ አየር ማረፊያ አግኝቷቸው ያየውን የሰማውን እጥር ምጥን ባለው የለመድነው መረጃ አቀባበል እንካችሁ ብሎናል ። የአብርሃ እማኝነት አስደስቶኝ እኔም ለዛሬ ወግ ዳሰሳ አበቃሁት ! ወዳጃችን አብርሃ ደስታ ሆይ ! የአረብ ሃገሩ የብዙሃን የኮንትራት ሰራተኞች አስከፊ ህይዎት ያጫዎቱህ ወደ ሃገር ለመግባት የታደሉት መሆናቸውን አስረግጨ እነግርሃለሁ ! ያየሃቸው የታደሉት ጥቂት ምሳሌዎች ናቸው ! የመንግስት ተወካይ አለን ለማለት አልደፍርም ! እውነቱ ይህ ነው ! አንተም እንኳን ከግፉአኑ ሰምተህ አሰማህን ! ይህ የማናችንም ሃላፊነት መሆን ሲገባው እያደረግነው አይደለም! የእህቶቻችን ህይዎት በአረብ ሃገር ምስክርነቱ ይህ ነው ! እንዲህ ይኖራል ! የእኔን በዚህ ላብቃና እጥር ምጥን ወዳለችው የአብርሃ ደስታን እማኝነት ከዚህ በታች እንድትመለከቱ ስጋብዝ ለአብርሃ ምስጋና በማቅረብ ጭምር ነው! እነጰ አበቃሁ ! ቸረወ ያሰማን !
    ነቢዩ ሲራከ
    By Abraha Desta የኢትዮዽያውያን ህይወት በዓረብ ሀገሮች ——————————————— ሮብ ነሓሴ 15, 2005 ዓም ጠዋት ቦሌ ኤርፖርት ነበርኩ። ኢንተርናሽናል ተርሚናሉ ከዓረብ ሀገራት በተመለሱ እንስት ኢትዮዽያውያን ተጥለቅልቋል። የተከፉና የተረበሹ ይመስላሉ። ከሰዓት በኋላ ወደ መቐለ ለመመለስ ወደ ሀገር ውስጥ ተርሚናል ገባሁ። ከነዚህ ጠዋት ረጅም ሰልፍ ይዘው ያየኋቸው ተመላሾች የተወሰኑ አገኘሁ። ስለ ህይወታቸው፣ ስለሚደርስባቸው እንግልት ወዘተ አጫወቱኝ። በዓረብ ሀገሮች የሚኖሩ ኢትዮዽያውያን እንደሰው አይቆጠሩም፤ ብዙ አካላዊና ስነ አእምራዊ ችግር ይደርሳቸዋል። ብዙዎቹ አብደዋል፣ ራሳቸው አጥፍተዋል። ኢትዮዽያውያን በመሆናቸው ራሳቸው ይረግማሉ፤ በመፈጠራቸው ያዝናሉ። የኢትዮዽያ ኤምባሲ ግን ምንድነው የሚሰራው? የዜጎች ደህንነት መጠበቅ’ኮ የመንግስት ሐላፊነት ነው። የኢትዮዽያውያን ስደትና ግፍ ሀገራችን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ሊመራት ይችላል።
    Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=6634

    Thursday, August 22, 2013

    እኔ ከሞትሁ ሰርዶ አይብቀል’ – ልንዋጋው የሚገባ አህያዊ ብሂል!

    እኔ ከሞትሁ ሰርዶ አይብቀል’ – ልንዋጋው የሚገባ አህያዊ ብሂል! – By Nasrudin Ousman በኢሕአዴግ የሚመራው መንግሥት በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና ክርስቲያኖች መካከል የእርስ በርስ ጥርጣሬና ጥላቻ ለመፍጠር፣ ከተሳካም የሃይማኖት ግጭት ለመቀስቀስ በተለያዩ አቅጣጫዎች በጣም አደገኛና መርዘኛ የሆነ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ከፍቷል፡፡ “እኔ ከሞትሁ ሰርዶ አይብቀል” በሚል አህያዊ ብሂል ላይ የተመሠረተውን ይህንን እርኩስ ዘመቻ፣ ለዚህች አገር ህዝቦች ሰላምና ፍቅርን የሚመኝ ኢትዮጵያዊ በሙሉ አጥብቆ ሊዋጋው ይገባል፡፡ … እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ያነሳናቸውና ተገቢ ምላሽ ያገኙ ዘንድ በሰላማዊ መንገድ የምንታገልላቸው ጥያቄዎች፣ መንግሥት በሃይማኖታችን ላይ የቃጣውን ዓይን ያወጣ ጣልቃ ገብነት መነሻ አድርገው የተነሱ እንጂ ድንገት ከመሬት ላይ የበቀሉ አይደሉም፡፡ [ከቶውኑ ድንገት ከመሬት ላይ የበቀሉ ጥያቄዎች የድፍን አገሪቱን ሙስሊሞች በአንድ መንፈስ በጋራ ሊያነቃንቁ ይቻላቸዋልን? ይህ የማይመስል ነገር ነው፡፡] … መንግሥት ከ1987 አጋማሽ አንስቶ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) ላይ ያሻውን ሰው ሲሾም እና ተቋሙን በካድሬዎቹ ሲያሽከረከር እየታዘብን በዝምታ አሳልፈናል፡፡ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለህዝበ ሙስሊሙ ምንም የረባ መንፈሳዊም ሆነ ማኅበራዊ አገልግሎት የመስጠት ብቃት እንደሌለው፣ በህዝበ ሙስሊሙ ስም በተቋሙ የሚንቀሳቀስ የህዝብ እና የአገር ሀብት በአሳፋሪ ሁኔታ በግለሰቦች ሲመዘበር፣ በሐጅና ዑምራ ጉዞ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ ከፍተኛ ብዝበዛ (ዝርፊያ) ሲፈፀም፣ የአርባ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ተቋም የሠፈር ዕድር እንኳ ለመምራት በማይበቁ መደዴ ግለሰቦች ሲመራ … ልባችን በሐዘን እየደማም ብዙ ዓመታትን በዝምታ አሳልፈናል፡፡ ይህ ሁሉ ሲኾን፣ ከዚህ የተቋማችን አሳዛኝ ገፅታ ጀርባ የኢሕአዴግ እጅ እንዳለ ሳናውቅ ቀርተን አልነበረም፡፡ … መንግሥትን “በቃህ!” ለማለት የተገደድንበት ሁኔታ የተከሰተው ኢሕአዴግ ይህንኑ ተቋማችንን መሣርያ በማድረግ በአዲስ አስተምህሮ ሊያጠምቀን መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ ማድረግ ከጀመረበት ከሐምሌ 2003 ወዲህ ነው፡፡ [… ይህ በስፋት የሚታወቅ በመሆኑ እዚያ ላይ ሀተታ አላበዛም፡፡] የሰላም ዘቦች እሥር እና ግልብ “ፀረ-አክራሪነት” እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ባይኖረን ኖሮ፣ እንደ ተቋም አልባነታችን ከዓመታት በፊት ወደ አስከፊ የጥፋት መንገዶች ለመነዳት በተዳረግን ነበር፡፡ በእርግጥም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መሪ አልባ ሁነው በቆዩባቸው ባለፉት አሥራ ዘጠኝ ዓመታት የሃይማኖት ጽንፈኝነት እና ነውጠኝነት ሊስፋፉ የሚችሉባቸው ብዙ ክፍተቶች ነበሩ፡፡ እነዚህን ክፍተቶች የደፈናቸው የነቀዘው መጅሊስ ሳይሆን፣ ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ውስጥ የበቀሉ በሳል አንጋፋና ወጣት የሃይማኖቱ ምሁራን ናቸው፡፡ በተለያዩ መድረኮች፣ እንዲሁም የትምህርትና መረጃ ማሰራጫ አውታሮች (መጻሕፍት፣ መጽሔት፣ ሲዲ፣ ወዘተ.) በሃይማኖት መቻቻልና ከሌሎች ሃይማኖት ተከታዮች ጋር አብሮ በመኗኗር፣ የጎረቤትን ሐቅ (መብት) በመጠበቅ አስፈላጊነት፣ የጽንፈኛ አስተምህሮቶችን ጉድፍ እና አሉታዊ ገፅታ በማጋለጥ እነዚህ ወጣት እና አንጋፋ ምሁራን ሙስሊሙን ማኅበረሰብ በትጋት አስተምረዋል፡፡ እነዚህ አንጋፋና ወጣት የሃይማኖቱ ምሁራን በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 27 የተደነገገውን “የሃይማኖት፣ የእምነትና የአስተሳሰብ ነፃነት” በመጠቀም ለኢትዮጵያ ሙስሊም ማኅበረሰብ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ህይወት መበልፀግ፣ እንዲሁም ህዝበ ሙስሊሙ ከሌሎች ሃይማኖት ተከታዮች ጋር በሰላም፣ በፍቅር እና በመከባበር የመኖር እሴትን በጥልቀት ተገንዝቦ ይህን እሴቱን እንዲንከባከብ በማስተማር ባይተጉ ኖሮ ኢትዮጵያዊው ሙስሊም በተለያዩ ኃይሎች ተፅዕኖ ውሉ በማይታወቅ አቅጣጫ የዕውር ድንብር በተጓዘና በተጋለበ ነበር፡፡ በእርግጥም የኢሕአዴግ መንግሥት ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ በኩል የሃይማኖት ጽንፈኝነት የሚያሰጋው ቢሆን ኖሮ፣ በኢትዮጵያዊው ሙስሊም ማኅበረሰብ ውስጥ የሰላምንና የአብሮ መኖር እሴቶችን ያሰረፁትን እነዚህን ድንቅ የማኅበረሰቡ አባላት (የሃይማኖት ምሁራን) በአጋርነት በማሰለፍ ስጋቱን በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያስወግድ ውጤታማ ሥራ መሥራት በቻለ ነበር፡፡ የሁከት ናፍቆት እጅግ የሚያሳዝነውና በአሁኑ ወቅት በገሃድ የሚታየው ግን፣ የኢሕአዴግ መንግሥት ፍላጎት በአገሪቱ ላይ ሰላምንና የህዝቦች አንድነትን ማስፈን አለመሆኑ ነው፡፡ ኢሕአዴግ የአገር ሰላምን እና የህዝቦችን በሰላም አብሮ የመኖር ትሩፋት በጽናት ሲሰብኩ የኖሩ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ወጣትና አንጋፋ የሃይማኖት ምሁራንን ዘብጥያ የወረወረው ከሰላም ፍፁም ተቃራኒ የሆነ እኩይ አጀንዳ በማንገቡ መሆኑ አሁን ግልፅ ሆኗል፡፡ ፍላጎቱ ሰላም ባለመሆኑም ነው፣ አልሳካልህ ያለውን ጽንፈኝነት ለመፈብረክ ነጋ ጠባ የሚደክመው፡፡ የህዝቦች ተፈቃቅሮ እና ተከባብሮ መኖር አልዋጥልህ ቢለው ነው ጽንፈኝነትን እና ሽብርን በዶኩመንታሪ ፊልም ለማቀናበር አለቅጥ ደፋ ቀና የሚለው፡፡ … የህዝቦች በሰላም መኖር፣ ሰላም ቢነሳው ነው በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና ክርስቲያኖች መካከል ጥላቻን ለመዝራት፣ ሁከትና የእርስ በርስ ግጭትን ለመጋበዝ ያለ አንዳች ኃፍረት በዘመቻ መልክ መንቀሳቀስ የጀመረው፡፡ … … ዛሬ አመሻሽ ላይ አንድ ወንድሜ “ኢትዮጵያን ዳያስፖራ” የተሰኘ አሜሪካ ውስጥ የሚሰራጭ የራዲዮ ጣቢያ በቅርቡ ካሰራጫቸው ዝግጅቶች የቀዳቸውን የተወሰኑ ድምፆች ልኮልኝ ሳደምጥ የተረዳሁት ይህንን እና ይህንን ሐቅ ብቻ ነው፡፡ የኢሕአዴግ መንግሥት እና አጫፋሪዎቹ ለዚህች አገር እና ለህዝቧ ምን እየደገሱለት እንደሆነ ማሰብ በጣም ይዘገንናል፡፡ ምን ያህል አቅላቸውን ቢስቱ ይህንን ለማድረግ እንደወሰኑ ለእኔ ፈጽሞ ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ምን ያህል አዕምሯቸው ማሰብ ቢሳነው ነው የዚህ ተግባራቸውን ውጤት አስከፊነት ለመገመት ያልቻሉት ለሚለው ጥያቄዬ ፈጽሞ መልስ ላገኝለት አልቻልኩም፡፡ ሃይማኖትን በመሰለ ለሰዎች ስሜት እጅግ ቅርብ በሆነ ጉዳይ ላይ እንዲህ ያለ መርዘኛ የጥላቻ እና የግጭት ቅስቀሳ ያውም በራዲዮና በድረ ገፅ ማሰራጨት እንደምን ለአገር ሰላም አሳቢ ሊያሰኝ እንደሚችል አላውቅም፡፡ ከዓመታት በፊት በአንድ የአገሪቱ አካባቢ በተፈጠረ ሃይማኖት ነክ ሁከት ላይ ‹‹እንዲህ እና እንዲያ አደረጉን›› የሚሉ የሰዎችን ስሜት በመጥፎ መልኩ የሚኮረኩሩ መልዕክቶችን ማሰራጨት እውን ለአገር ሰላም ከማሰብ የመነጨ ነውን? … የመንግሥት ሥልጣን ከስኳር እንደሚጥም ቢያንስ መገመት አያቅተኝም፡፡ ፖለቲከኞች ከጠላት ጋር የሚደረግ ጦርነትን ለሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያነት እንደሚጠቀሙባትም አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን በሥልጣን ላይ ለመቆየት ሲባል ለረዥም ጊዜ ሊገዙት የሚሹትን የራስን አገር ህዝብ በሃይማኖት ለማጋጨት ታጥቆ መነሳት፣ ፖለቲካዊ ጥበብ ሳይሆን “እኔ ከሞትሁ ሰርዶ አይብቀል” ያለችውን አህያን መሆን ይመስለኛል፡፡ አላህ ከአህያነት ይጠብቀን!! ኢሕአዴግ ህዝበ ክርስቲያኑን ከሙስሊሙ ጋር ለማጋጨት ታጥቆ በተነሳበት በአሁኑ ወቅት ከወደ አሜሪካ እንዲህ ያለ መርዘኛ ፕሮፖጋንዳ በራዲዮና በድረ ገፅ መሰራጨቱ፣ አገራችን እና ህዝቧ ምን ያህል ከባድ አደጋ እንደተደቀነባቸው በግልፅ ያሳያል፡፡ ምንም እንኳ እንዲከሰት የሚናፍቁት የህዝቦች የእርስ በርስ ግጭት ቢከሰት (በአክራሪ እና በጽንፈኛ ዲስኩራቸው) ሙስሊሙን ተጠያቂ ለማድረግ እንደሚንደረደሩ ግልፅ ቢሆንም፣ አደጋው ግን በሙስሊሙ ላይ ብቻ የተደቀነ አለመሆኑን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ክርስቲያኑም ጭምር በውል ሊገነዘበው ይገባል፡፡ በዚህ ግንዛቤ ላይ በመመሥረትም፣ ይህን በእኛ በኢትዮጵያውያን ላይ የተደቀነ ወቅታዊ አደጋ ወይም ፈተና፣ የረዥም ዘመናት አብሮ መኖር ባስተማረን ትዕግስት፣ ብልሀትና ጥበብ በአሸናፊነት ለመወጣት የየድርሻችንን ኃላፊነት እንወጣ እላለሁ፡፡ ይህንንም ለማድረግ የኃያሉን ፈጣሪያችንን እገዛ እማፀናለሁ፡፡ … ላለፉት ሁለት ዓመታት እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም፣ በሚሊዮኖች ከሚቆጠሩ የእምነት ወንድምና እህቶቼ ጋር ለሃይማኖት ነፃነቴ መከበር በሰላማዊ መንገድ እየታገልኩኝ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ነገር ግን የሃይማኖት ነፃነቴ መከበር ከሚያስጨንቀኝ ባላነሰ፣ ምናልባትም በበለጠ የኢሕአዴግ መንግሥት ህዝበ ክርስቲያኑን ከሙስሊሙ የማጋጨት ዕኩይ ሤራ ያስጨንቀኛል፡፡ እናም በአላህ ፈቃድ እና እገዛ ይህንን ዕኩይ ሤራ እስከ መጨረሻው አምርሬ እታገላለሁ፡፡ ለእኔ ከዚህ በላይ ኢትዮጵያዊነት የለም፡፡ … ቅኑን መንገድ በተከተሉ ሁሉ ላይ ሰላም ይስፈን፡፡ የዓለማት ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ከክፋት ኃይሎች ክፋት ይጠብቅልን፡፡ አሚን፡፡ _______________________ *መልዕክቴን ከተጋራችሁት፣ በሰሌዳችሁ ላይ ለሌሎች ብታጋሩት ደስ ይለኛል፡፡ አመሰግናለሁ፡፡

    33ቱ የተቃዋሚ ፓርቲ ስብስብ ሰማያዊ ፓርቲን አባረናል አሉ


    አቶ ይልቃል ጌትነት - የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር

    የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ይልቃል ጌትነት ለጋዜጦች የሰጧቸው አስተያየቶች “…ለሌሎች ፓርቲዎች ክብርና ዕውቅና የነፈገ ነው…” ሲሉ የሰላሣ ሦስቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብስብ ቅሬታውን ገልጿል።
    በዚህም ምክንያት ፓርቲው ከተቃዋሚዎች ስብስብ እንዲሰናበት መወሰኑን ገልጿል።
    “አቶ ይልቃል በበኩላቸው ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ በሰጡት ቃል የሰጠሁት አስተያየትና ያንፀባረቅኹት ሃሣብ አዲስ አይደለም፣ እውነትም ነው” ብለዋል።
    ለዝርዝሩ የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡
    http://amharic.voanews.com/audio/Audio/318005.html

    Anti-terrorism decree: Born from power thirst

    Anti-terrorism decree: Born from power thirst
    Wednesday, August 21, 2013
    by Reeyot Alemu, Ethiopia
    The article has been translated from the Amharic original for the International Women Media Foundation. The author,
    a columnist for the now-defunct Ethiopian newspaper Feteh, is currently serving a 5-year prison sentence in Addis Ababa on bogus terrorism charges. The International Women’s Media Foundation honored Alemu with its 2012 Courage in Journalism Award last year, and in May 2013, the UNESCO recognized her “commitment to freedom of expression” with its Guillermo Cano World Press Freedom Prize.
    Many questions cross my mind when I look at the “‘Anti-Terrorism Decree” and its application. Why does this decree have paragraphs that violate human rights? Why does it prosecute innocent citizens who have no ties to terrorism or terrorist organizations? I ask myself. In order to answer these questions one needs to look at the reasons behind the creation of such a decree, and so I did.
    Why was the anti-terrorism decree written? One needn’t look too far to realize that the ruling party, EPRDF, didn’t create these anti-terrorism laws because it faced a real threat. You only need to look at the individuals who are either facing such charges, or have already been found guilty under this decree. Members of the opposition party who have denounced human rights violations and have peacefully called for the replacement of the current regime by a more democratic one, freethinkers who dared ask stern questions to officials at locally organized discussion forums, leaders of the Muslim community who refused to dilute and redraft their religious beliefs to appease the government’s stance on religion, and ourselves, members of the free press who performed their duty as voices of the people have been the main victims of this anti-terrorist decree.
    This proves that the real purpose of this decree is to enable the current regime to comfortably rule without any criticism, opposition, or competition. These actions are not creations of the EPRDF, instead they are old tried and true methods copied from other brutal regimes. It is very well known that colonial regimes of the past found it convenient to label the freedom fighters that refused to kneel as “terrorists.” And today, the EPRDF travels this same colonial path by stuffing its prisons with its own citizens and punishing those of us who have refused to give up our human and citizenship dignity.
    What is to be done? Stopping the gross human rights violations that the EPRDF is committing under the guise of the anti-terrorism decree requires a lot of work. The current anti-terrorism decree will have to be replaced by a more appropriate one. Even with such changes, as long as the judicial system leans in favor of the EPRDF such arrests will continue. For, those of us who are currently imprisoned would have been found “not guilty” had we been judged fairly, even under the current anti-terrorism decree. As such, demonstrations and movements aimed at this decree, and more importantly at the ruling EPRDF who seeks to illegally use it, shall be strengthened and continued.
    The reason I strongly believe that these protests should primarily be aimed at the ruling party is because it is the source of the wrongful application of this law and other innumerable Ethiopian problems. We have observed with disgust the length this regime will travel to protect its grip on power, and its rule. In other words, the actions of the EPRDF are based on motives that are tied to ethnicity, power hunger, and unjust prosperity among others. In Arthur Gordon’s words “If one’s motives are wrong, nothing can be right.” Because of this, nothing good can be expected from the EPRDF.
    Therefore our only option for change remains a modern and peaceful struggle wherein we should be prepared to provide the needed sacrifices. As we embark on this journey to transform the system, there are many related issues that we should consider. We should deeply consider all the challenges set forth by the ruling party whether they are the ethnic, religious, ideological, or the interest based divisive elements it nourishes. We shall learn how to unite our many fronts of struggle into one.
    Looking forward, it is the role of any responsible citizen, and especially that of the opposition parties and related groups, to think of and discuss the nature of the system that shall proceed the current one. For as long as we accomplish these required duties, and stay firm in our convictions, a Bright Day will not be too far.

    Ethiopia: African Media Leaders Must Boycott Ethiopia

    By Fasil Girma Aragaw

    Ethiopian journalists have come to expect the worst from our government
    August 22, 2013 (Indepth Africa) — One of the world’s most hostile governments to an independent press, it has jailed friends and colleagues, forced them to leave the country and unjustly branded them as terrorists or enemies of the state for doing their jobs. But until now we have at least been able to count on the moral support of fellow journalists, media organizations and others opposed to injustice.
    That has been changed by the deeply disappointing decision of the African Media Initiative (AMI) to hold its annual convention, the African Media Leaders’ Forum, in Addis Ababa this year. Far from helping to improve Ethiopia’s media environment, as suggested by the AMI’s chief executive, Amadou Mahtar Ba, this move will instead embolden the government in its ongoing war against the press.
     
    According to the Committee to Protect Journalists, at least 49 Ethiopian journalists have been forced into exile since 2007. Nine of our colleagues languish in prison, making the country the second worst jailer of journalists in Africa after Eritrea.
    Just last year, the government forced the closure of Feteh (“Justice”), the prominent independent newspaper in Addis Ababa, because of its critical editorial line. Its publisher, Mastewal Berhanu, who was forced to leave the country after receiving threats from security agents, is one of those who have said that the AMI’s decision is a blow to jailed and exiled Ethiopian journalists.
    We have held the AMI in high esteem because of its stated commitment to”promote the development of pluralistic media”. But we believe its justification for holding the forum in Ethiopia is self-serving and insensitive to Ethiopia’s independent media community, and we cannot understand why Mr. Ba calls the decision “courageous”.
    The AMI’s suggestion that holding the forum in Addis Ababa will further a process of “constructive engagement” with media stakeholders, including the government, is either naïve or aimed at benefitting narrow interests that do not really serve the Ethiopian media community at large. Neither the publishers’ association nor the media council with which the AMI has interacted represent independent journalists, nor do they defend their rights.
    Despite all the Ethiopian government’s actions to stifle press freedom, I used to believe that if the press could organize itself it could gain enough strength to overcome its multi-faceted challenges. To test my belief in practice, I tried in 2011 to organize a monthly informal journalists’ roundtable, bringing the highly-polarized media together to discuss investigative journalism, particularly on corruption issues.
    This platform sought to help the media play its watchdog role and I hoped it would grow into an investigative or anti-corruption journalists’ association.
    But over ten months of meetings, the arrest and intimidation of journalists, along with the closures of local rights groups, rendered members frustrated and hesitant about forming an independent association.
    Even the monthly roundtable meeting could not be sustained as participants gradually dropped out. Stringent laws, arrogant bureaucracy, threats and other challenges sapped the media of its energy, leaving it too weak to build one strong local media association which could help protect itself.
    Today, professional media associations are either under the concealed patronage of the government or too scared to speak out for unlawfully imprisoned journalists such as Eskinder Nega, Reeyot Alemu, Woubshet Taye and many others. The Ethiopian government has ensured that there is no strong and vibrant media association that can stand for freedom of speech and press freedom.
    Mr. Ba’s suggestion that the government-sponsored media council “is known for its independence and commitment to building free and balanced media” confirms our fears that the AMI, its handful of local partners and the Ethiopian government are speaking with one and the same voice.
    I appreciate the Pan-African approach of Mr. Ba. But Pan-Africanism begins with African solidarity, based on the understanding that injustice against one African is an injustice against all Africans. The Ethiopian government is willing to have the AMLF meet in Addis Ababa because it can use the event as a counter to international pressure for freedom of speech and press freedom.
    In our struggle to realize the freedoms promised in our constitution, Ethiopian journalists have seldom heard African intellectuals, media leaders or the African Union call out our government on its grave abuses and support those struggling to be free. Apartheid and colonialism were not defeated with “constructive engagement” or apathy and silence.
    Business interests that worked with the apartheid regime are marked with shame forever. The AMI should reconsider its plan to hold the meeting in Addis Ababa.