Sunday, November 17, 2013

በጅዳ ሳኡዲ አረቢያ፤ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ስራውን አቆመ(The Ethiopian Consulate in Jeddah closes its doors)በኢትዮጵያውያን ላይ ሲደርስ የነበረውን ግፍ እና መከራ መከላከልም ሆነ ማስቆም ያልቻለው፤ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽቤት ከዛሬ ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ስራውን ያቆመ መሆኑን ገልጿል።ከምንግዜውም በላይ አሁን ስራውን መስራት ይገባው የነበረው፤ አቅሙን አጠናክሮ ለኢትዮጵያውያን መብት በመቆም ስራ መስራት ይገባው የነበረው ቆንስላ በዚህ ቀውጢ ወቅት አገልግሎት መስጠት መቆሙ ብዙዎችን አሳዝኗል።

በኢትዮጵያውያን ላይ ሲደርስ የነበረውን ግፍ እና መከራ መከላከልም ሆነ ማስቆም ያልቻለው፤ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽቤት ከዛሬ ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ስራውን ያቆመ መሆኑን ገልጿል።ከምንግዜውም በላይ አሁን ስራውን መስራት ይገባው የነበረው፤ አቅሙን አጠናክሮ ለኢትዮጵያውያን መብት በመቆም ስራ መስራት ይገባው የነበረው ቆንስላ በዚህ ቀውጢ ወቅት አገልግሎት መስጠት መቆሙ ብዙዎችን አሳዝኗል።
ይህ ከዚህ በታች ያለው ማስታወቂያ በጽ/ቤቱ መግቢያ ላይ የተለጠፈ ማስታወቂያ ሲሆን፤ ሌሎች የአካባቢው ምንጮች ቀደም ብለው እንደገለጹት ከሆነ፤ “የቆንስላ ጽ/ቤቱ ስራውን ካቆመ ቆይቷል። በተለይም አንዳንዶቹ ሰራተኞች፤ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱት ሰዎች ጋር አብረው ሄደዋል” ሲሉ ተቃውሟቸውን ሲገልጹ ነበር የሰነበቱት። አሁን ዛሬ የተደረገውን የስራ ማቆም ማስታወቂያም፤ አብዛኞቹ ሰራተኞቹ ወደ አዲስ አበባ ተደባልቀው በመመለሳቸው የሚለውን አባባል ያጠናክረዋል።
ከዛሬ ጀምሮ፤ አገልግሎት መስጠት አቁመናል!! 
ከዛሬ ጀምሮ፤ አገልግሎት መስጠት አቁመናል!! 
ነዋሪነቱ በጅዳ፣ ሳኡዲ አረቢያ የሆነው ነብዩ ሲራክም እንዲህ ብሏል። “በጅዳና አካባቢ እየሆነ ስላለው አጠቃላይ ሁኔታ ከመንግስታችን ተወካዮች መረጃ ማግኘት አልችል ያለው ነዋሪ ተረባብሿል … ህገ ወጥ ነዋሪዎች ወደ ሃገር ቤት መግባት የሚችሉበትን ቀዳዳ ሁሉ ቢያነፈንፉ የመረጃ ፍንጭ ሊያገኙ እንዳልቻሉ ይናገራሉ! አንዳንደዶች ደግሞ እየተቆጡ ነው! ህጋዊው ነዋሪ ዜጎቹን መደገፍ የሚችልበት መንገድ ጠፍቶት እየዋለለ ነው! ከትናንት ጀምሮ ከአንዳንድ ወዳጆቸ ጋር ጉዳዩን በዋናነት የሚያንቀሳቅሱትን የመንግስት ተወካዮች ድጋፍ ማድረግ ባለብን እርዳታና ድጋፍ ዙሪያ ለመምከር ቀጠሮ ይዘናል! ረፋዱ ላይ ደግሞ የጅዳ ቆንስል ስራ በውል ላልተጠቀሰ ጊዜ አገልግሎት መስጠት እንዳቆመ በማስታወቂያ አስታውቋል ! ግራ ግብት ያለ ነገር ሆኖብናል!” በማለት አስተያይውቱን ሰጥቷል።

No comments:

Post a Comment