Wednesday, November 6, 2013

የኢንተርኔት አፈናንና ስለላን የሚፈቅደው አዋጅ ሀሙስ ይጸድቃልጥቅምት ፳፯(ሃያ ሰባት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሚኒስትሮች ምክር ቤትን ደንብ ቁጥር 250/2003 ሽሮ እንደገና ለማቋቋም የተዘጋጀ ፤ ተጠሪነቱ ለጠ/ሚኒስትሩ የሆነ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን ለማቋቋሚያ

የኢንተርኔት አፈናንና ስለላን የሚፈቅደው አዋጅ ሀሙስ ይጸድቃል

ጥቅምት ፳፯(ሃያ ሰባት )ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :- የሚኒስትሮች ምክር ቤትን ደንብ ቁጥር 250/2003 ሽሮ እንደገና ለማቋቋም የተዘጋጀ ፤ ተጠሪነቱ ለጠ/ሚኒስትሩ የሆነ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን ለማቋቋሚያ
የወጣው አዋጅ ሀሙስ ይጸድቃል።በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ተዘጋጅቶ በካቢኔ ፀድቆ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ኮምፒዩተርን መሰረት ያደረጉ የትራንሰፖርት እና የኢንዱስትሪ የቁጥጥር ስርዓቶች ደህንነት ኮምፒዩተርን መሰረት ያደረጉት የኢነርጂ፣ የባቡር ኔትዎርክ፣ የአቬሽን፣ የውሃ አቅርቦት ወዘተ የቁጥጥር ስርዓቶች ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል መደንገጉን ይገልጻል።
የሳይበርና የኤሌክትሮኒክ ሚዲያ ደህንነት የሳይበር እና የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች የኢንተርኔት ራዲዮ፣ ኢንተርኔት ቲቪ፣ የቲቪና የሬዲዮ አገልግሎቶች፣ ማህበራዊ ሚዲያዎች፣ ዌብ ሳይቶች፣ ብሎጎች ወዘተ የሚያጠቃልል ሲሆን፤ ተደራሽነቱ ለሁሉም እኩል በመሆኑ
ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማት ካለው ፋይዳ በተቃራኒ ለጦርነት ቅስቀሳ፣ ለስም ማጥፋት ዘመቻ፣ የሃገርን ገጽታ ለማጉደፍ፣ ፀረ ልማት ፕሮፖጋንዳዎችን ለማሰራጨት፣ ፍርሃትንና አሉባልታን ለመንዛት፣ የኢኮኖሚ ስፔኩሌሽን ለማሰራጨት ወዘተ መጠቀሚያ ሊውሉ እንደሚችሉ ህጉ ይዘረዝራል።
ኮምፒዩተርን መሰረት ያደረገው ወታደራዊ የእዝና የቁጥጥር ስርዓት ደህንነት በመላ ሃገሪቱ ዳር ድንበር ላይ የመሸገው የሃገር የመከላከያ ኃይል እየዘመነ መሄዱ እና ኮምፒዩተርን መሰረት
ባደረገው የእዝና የቁጥጥር ስርዓት ላይ መመራቱ ተገቢ እና አዋጪ መሆኑ አያከራክርም የሚለው አዋጁ፣   በመሆኑም ኮምፒዩተርን መሰረት ያደረጉት መሰረተ ልማቶች ደህንነት መጠበቅ ማለት ወታደራዊው የእዝ እና የቁጥጥር ስርዓቱ ደህንነት መጠበቅ ማለት ነው ብሎአል። ይሁንና ኮምፒዩተርን መሰረት ያደረጉ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰው ማንኛውም አደጋ በወታደራዊ የእዝ እና ቁጥጥር ስርዓቱ ላይ የሚደቀነው አደጋ መኖሩን የሚገልጸው አዋጅ፣  ይህ በብሄራዊ ደህንነት ላይ በቀጥታ የሚሰነዘር ጥቃት በአንድ በኩል ኮምፒዩተርን መሰረት ያደረጉ መሰረተ ልማቶች በመጠበቅ በሌላ በኩል ደግሞ ኮምፒዩተርን መሰረት ያደረገው
ወታደራዊውን የእዝ እና ቁጥጥር ስርዓቱ በልዩ ሁኔታ መጠበቅ እንደሚያስፈልግ ያትታል። አዲሱ ህግ መንግስት ዜጎቹ በኢንተርኔት የሚያደርጉትን ማንኛውንም አይነት ግንኙነት ለመቆጣጠር የሚያስችለው ሲሆን፣ የቴሌኮሚኒኬሽን መስሪያ ቤትን ብቃት ለማሳደግ ከፍተኛ ባጀት እንደሚመደብም ያትታል።

No comments:

Post a Comment