Monday, November 11, 2013

ሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ስላለው ህልፈተ ህይወት መንግስት የሚጠበቅበት እንዲወጣ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ አሳሰቡ Posted: November 11, 2013 የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ እየታካሄደ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዞን ምክር ቤት 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በመገኘት በሀገራችን ኢትዮጵያ ባለው የፖለቲካ፤ የዲሞክራሲ እና የፍትህ እጦት እንዲሁም ሁሉንም ኢትዮጵውያንን የሚያሣትፍ የኢኮኖሚ እድገት ባለመኖሩ ምክንያት ብዙ ዜጎች ወደ ደቡብ አፍሪካ ሃገራትና ወደ አረብ ሀገራት በእግር ሳይቀር ለመሰደድ ከመገደዳቸው በተጨማሪ በጉዞ ወቅት በአውሬ መበላት በበሽታ መሞትና ለአስገድዶ መደፈር መዳረጋቸውን አውስተዋል በተላይ ከቅርብ ግዜ ወዲህ የሳውዲ አረቢያ መንግስት በኛ ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለው ስቃይና እንግልት ሳያንስ እስከመግደል የሚያድርስ እርምጃ በመወሰዱ የበርካታ ኢትዮጵውያን ህይወት እየተቀጠፈ እንደሚገኝ ለማወቅ ችለናል በመሆኑም በሀረብ ሀገራት ለስራ ተሰደው በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ህልፈተ ህይወትና ጉዳት ፓርቲውን በእጅጉ እንደሚያሳስበውና ለዚህም በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በአፋጣኝ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ በማለት አሳስበዋል:: በመጨረሻም ለተጠቂ ቤተሰቦች የተሰማቸውን ሀዘን በመግለፅ ይሔ ግፍና ጭቆና እንዲቀር ፍትህና ዲሞክረሲ እንዲረጋገጥ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡

1426366_605593059499529_213620200_n

No comments:

Post a Comment