Tuesday, October 1, 2013

ማን ይሁን እውነተኛ፡ ኢሳት ወይስ ሪፖርተር?

ኢሳትም አለ፥ 
                          BREAKING NEWS SEP 25, 2013

ESAT-Salsaywoyane
ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳም አሉ (ሪፖርተር)፥
salsaywoyane
ዝርዝሩን ከሪፖርተር ጋዜጣ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ … 
ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው! ነው የሚባለው እርስዎስ ምን ይላሉ? ማን ይሁን እውነተኛ፡ ኢሳት ወይስ ሪፖርተር? ከምንም በላይ የገረመኝ ግን ኢሳት ሰበር ዜና ሲል ያልተጣራ ዘገባ ማቅረቡ ሳይሆን ጣቢያው (ኢሳት) ለመዋሸት ካለው ችኩልነትና ፍጥነት የተነሳ የፈጸማቸው የሥርዓተ ነጥብና የፊደል ግድፈት ነው። ሥርዓተ ነጥብና የፊደል ግድፈት የሚፈጽም ሁሉ ውሸታም ነው እያልኩ እንዳልሆነ አንባቢ ይረዳኛል የሚል እምነት አለኝ። አልፎ አልፎም ቢሆን የሥርዓተ ነጥብና የፊደል ግድፈት የማይፈጽም ማንም የለም። ታድያ አንድ ራሱን እንደ ተቋም የሚጠራ ድርጅት እንዲህ ዓይነቱ ተደጋጋሚ ጉልህ ስህተቶችን ሲፈጽም ግን ነገሩ አሳሳቢ ከመሆኑ አልፎ ተቋሙ ምን ያህል የሞያ ዝቅጠት አዘቅት ውስጥ መነከሩን የሚያሳይ፤ ተአማኝነት የሌለውና እምነት የማይጣልበት ዘርዛራ ወንፊት መሆኑ ጭምር አስረግጦ የሚናገር ነው።  መቼ ይህ ብቻ ሳይታሰሩ “ታሰሩ” ብሎ ዜና የሰራባቸው ግለሰብ አለመታሰራቸውን ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠታቸው እያወቀ ኢሳት ለፈጸመው ውንብድና ይቅርታ ለመጠየቅ እንኳ አልደፈረም።
ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል
Oct 1, 2013

No comments:

Post a Comment