Wednesday, October 2, 2013

13 ያህል ስደተኞች በጀልባ ሰምጠዉ መሞታቸዉ ተሰማ

0,,15761502_303,00
13 ያህል ስደተኞች በጀልባ ወደ ኢጣሊያ- ሲሲሊ የባህር ዳርቻ በዋና ለመድረስ ሲሞክሩ ሰምጠዉ መሞታቸዉ ተሰምቷል። ከጀልባ ወርደው በዋና ለመሰወር ሲሞክሩ ነው። የተባበሩት መንግሥትት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን በምህፃሩ UNHCR እንዳስታወቀው በኢጣሊያ በኩል የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋ ሲነፃፀር በ3 እጥፍ ጨምሯል።
ባለፈው ረቡዕ ነበር ከ700 በላይ ተገን ጠያቂ ስደተኖችን ያሳፈሩ ሶስትጀልባዎች ደቡብ ኢጣሊያ ሲሺሊ ግዛት የባህር ዳርቻ ገብተው የተገኙትየኢጣሊያ ጠረፍ ጠባቂ ዘበኖች ለኣጃንስ ፍራንስ የዜና ኣገልግሎት እንደደገለጹት ሁለቱ የመጡት በላምፔዱሳ ደሴት በኩል ነው በኢጣሊያ ደቡባዊ ጫፍ የምትገነው የላምፔዱስ ደሴት የማንነት
ማረጋገጫያልያዙ በርካታ ስደተኖች ወደ ኣውሮፓ የሚሸጋገሩባት ዋንና በር መሆንዋ ይነገርላታል ከስደተኖቹ መካከልም ገሚሶቹ የሶሪያ ዜጎች መሆናቸው ታውቀዋል በዘገባው መሰረት የመጀመሪያዋ ጀልባ ብቻ 398 የሶሪያ ስደተኖችን ይዛለች በሁለተኛው ጀልባ ላይ የነበሩት 111 ስደተኖች ማንነት ወደፊት ይጣራል ተብለዋል ። የመጨረሻዎቹ ደራሾች 350 ስደተኖችን ብቻ በምታስጠልል
የደሴቲቱ ጊዛዊ የስደተኖች ማቆያ ጣቢያ ውስጥ ተጨናንቀው እንደሚገኙም ለማወቅ ተችለዋል 200 ተሳፋሪዎችን የያዘችው ሶስተናዋ ጀልባ ባለፈው ማክሰኖ ነበር በቅንት ኣውሮፕላን ታይታ በሲሺሊው የሲራውኮውስ ወደብ እንድትጠለል የተደረገችው ከ200 ዎቹ ተሳፋሪዎች መካከል 70ዎቹ ህጻናት መሆናቸው ታውቀዋል
0,,15443578_4,00
የእነዚህ ጀልባዎች ኣመጣጥ የግጭት ቀጠና ከሆኑት የሜዲትራኒያን ባህር እና የኣፍሪቃ ቀንድ አካባቢዎች የሚመጡ ጀልባዎች ቁጥር በእጅጉ እየጨመረ መምጣቱን ያመለክታል ተብለዋል የ ተ መ ድ የስደተኖች ተቁዋም ባሳለፍነው ወር መጀመሪያ ላይ እንዳስታወቀው
ከ20000 በላይ ተገን ጠያቂ ስደተኖች ኢጣሊያ መድረሳቸው ሲታይ ይህ አኃዝ በ2012 እ ኣ,ኣ ማለት ነው በዓመቱ ከገቡት ስደተኖች በሶስት እጥፍ ማሻቀቡን ያመለክታልአብዛኖቹ የሚመጡት ደግሞ ከኤርትራ ሶማሊያ እና ሶሪያ መሆኑ ታውቀዋል ። የእነዚህ ጀልባዎች ጉዞ በራሱ ፈታን መሆኑን ብዙዎች በምሬት ይናገራሉ
በትላንትናው ዕለትም 13 ስደተኖች እጣሊያ ጠረፍ ከደረሱ በኃላ ከጀልባ ወርደው በዋና ለመሰወር ሲሞክሩ መሞታቸውን የአካባቢው ከንቲባ አስታውቀዋል አንዳንዶቹም ለጥቂት ተርፈው በኣካባቢው ወደሚገኝ ሆስፒታል የተላኩ ሲሆን ባለፈው ቅዳሜ 339 ስደተኞችን አሳፍራ ሲሲሊ እጣሊያ በደረሰች ጀልባ ላይም ኣንዲት የ 22 ዓመት የሲሪያ ዜጋ ሞታ መገነትዋ ተዘግበዋል ኣንዳንዴም ኢጣሊያ ጠረፍ ሲደርሱ ስደተኖች በባለጀልባዎቹ አማካኝነት ወደ ባህር የሚወረወሩበት ኣጋጣሚም እንዳለ ተወስተዋል
0,,16355204_404,00
የካቶሊክ ቄስ የሆኑት አባ ሙሴ ዘርዓይ THE AGENCY ABESHA የተባለ ግብረ ሰናይ ተቋዋ መሪ ናቸው ድርጅታቸው ከሊቢያ ተሳፍረው በኢጣሊያ በኩል የሚገቡ ስደተኖችን በማማከር እና በመርዳት ይታወቃልችግሩ ከስደተኖቹ አንጻር ሌላ ኣማራጭ አለመኖሩ ሲሆን የኣውሮጳ መንግስታትም በዚህ ረገድ ከልብ አላሰቡበትም ይላሉ አባ ሙሴ ። አባ ሙሴ እንደሚሉት በዚህ ዓመት ብቻ 100 ያህል ስደተኖች በተመሳሳይ ሁኔታ ህይወታቸውን ኣተዋል
ባለፉት ሶስት ሳምንታት ብቻ 1800 ያህል ስደተኖች በባህር መምጣታቸውን የጠቀሱት አባ ሙሴ በኣሁኑ ጊዜ 1500 ያህሉ በተለያዩ ካምፖች ይገኛሉ ብለዋል ይህንኑ ሁኔታ ለማስቆምም የኣውሮፓ ህብረት ኢጣሊያን ጨምሮ ከሊቢያ እና ቱኒዚያ መንግስታት ጋር በመሆን ሰብዓዊ የሆነ መፍትሄ መሻትይኖርበታል ሲሉ መክረዋል ።
ጃፈር አሊ
ሂሩት መለሰ
ሊንኩን በመንካት ዝርዝር ዘገባውን ያዳምቱ

No comments:

Post a Comment