Monday, January 20, 2014

ጎንደር ውስጥ አንድ ወታደር ሶስት ሰው ገደለ

Jan. 20, 2o14
በጎንደር አካባቢ ማክሰኝት በተባለች ከተማ አንድ የታጠቀ ወታደር የሺ ተሻገር ተባለች የሆቴል ባለቤት በሃይል ለመድፈር በሞከረበት ግዜ ባሰማችው የእርዱኝ ጩኸት በወቅቱ ለመርዳት የመጡ አቶ መንግስቱ፤ የሆቴሉን ዘበኛ ኣቶ ዳኛቸው አለባቸውንና የሆቴሉን ባለቤት የሆነችው ግለሰብ ቦንብ አፈንድቶ ገድልዋቸው እንደተሰወረ ለማወቅ ተችልዋል::

ግድያው በተፈፀመበት ወቅት በመዋቾች ቤተሰብና ባአካባቢው ህብረተሰብ ከባድ ግርግር በመከሰቱ ምክንያትም በንፁሃኑ ወገኖች ላይ እሰቃቂ የግድያ ወንጀል የፈጸመው ኣካል ሳይያዝ ማምለጡ ያካባቢው የፀጥታና ያስተዳደር ድክመት ውጤት ነው ብለው እየገለፁ መሆናቸው ታውቀዋል::

በተመሳሳይ ሁኔታ ከደብረ ማርቆስ ዩንቨርስቲ ሁለት ተማሪዎች በታህሳስ 29/2006 ዓ.ም ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በስለት ተገድለው መገኘታቸውና። ከነዚህም- ፍሮምሳ ሃይለስላሴና ግርማቸው መኳንንት እንደሆኑ ተገልፅዋል:: መረጃው በማስከተል በዩንቨርስቲው ተማሪዎች ላይ እየተፈፀመ ባለው ግድያ በከባድ ስጋት ላይ በመውደቃቸው ምክንያት፣ትምህርታቸውን በአግባብ እንዳይከታተሉ በማሸማቅቅ ላይ እንደሚገኙና፣ቤተሰቦቻቸውም ትልቅ ስጋት ላይ መውደቃቸውን መረጃው አስረድትዋል::

Source: ዴ.ም.ህ.ት

No comments:

Post a Comment