Thursday, January 16, 2014

ድርድሩ አልተሳካም፡ ተኩስ ተከፍቷል ህዝብ እየተደበደበ ነው

ፖሊሶች አራት የኗሪዎቹ ተወካዮች በሃይል ሲወስዱ የአፅቢ ህዝብም አስራ አራት ፖሊሶችና አንድ ምልሻ አግተው ነበር። ህዝቡ ፖሊሶቹ እንዲለቅ አስተዳደሩ ደግሞ አራቱ ተወካዮች እንዲለቅ ድርድር ተጀምሮ ነበር። በድርድሩ መሃል የወረዳው አስተዳደር አዲስ ሃይል በመጥራት (ከሌላ ወረዳና ከክልል አስተዳደር የፀጥታ ሃይሎች በመላክ) ህዝብ በተሰበሰበብት መተኮስ ጀመሩ (ከምሽቱ 2:30-2:56)። ምልሻዎቹና ወታደሮቹ የታገቱትን ፖሊሶች ለማስለቀቅ እስከ ሁለት መቶ (በኗሪዎቹ ግምት መሰረት) የሚደርስ ጥይት በመተኮስ የታገቱት ፖሊሶችን ማስለቀቅ ችለዋል። እስከ ሁለት ሺ የሚጠጋ ህዝብ ተሰብስቦ እየጨኸ ይገኛል። አሁን (ከምሽቱ ሦስት ሰዓት) ብዙ ምልሻዎች የጫኑ ብዙ መኪኖች ወደ አከባቢው እየገቡ ነው። በሌላ አቅጣጫ (በስተ ሰሜን በኩል) ደግሞ ሌሎች ብዙ መኪኖች እየገቡ ነው (ምልሻ ወይ ፖሊስ ወይ ወታደሮች መሆናቸው ግን በትክክል አይታወቁም)። ህዝብ በዱላ መደብደብ ጀምረዋል። ህዝቡ እየጮኸና ፈጣሪው እየለመነ ነው። የህዝቡ ጩኸትና ለቅሶ በስልክ መስማት ችያለሁ። እያናግሩኝ ያሉ ሰዎችም መረጋጋት ተስኗቸዋል። አሁን ከምሽቱ 3:05 ሁነዋል።
Abraha Desta

No comments:

Post a Comment