
አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው በነደፉት ዕቅድ መሠረትም ሦስት አውቶብሶችን (coaches) ለራሳቸው በመከራየት ከዛም የግብረ ሰዶማውያን ነጻነት (Gay right movement) አባሎች በተጨማሪ በሁለት አውቶብሶች (coaches) ላይ በመሆን በድምሩ አምስት አውቶብስ ሙሉ ሰውን በመያዝ የተቃውሞ ትዕይንቱን ለማካሄድ መስማማታቸውን በቅጽል ስሙ Endexye የሚባለውና ትክክለኛ ስሙ እንዳለ ወንዳፍራሽ የተባለው ግለሰብ ካሰራጨው የtext መልዕክት ለማረጋገጥ ተችሏል።
የቴክስቱም ቀጥተኛ ቅጂ ቀጥሎ የተመለከተው ነው።

Respond from Dicon Mengesha Melke “Endex complaining to the university were Wondimu work should be practical because he damage the image of our church and the biography of our fathers and sisters.”

ይህ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስከፊ ስድብ ከመሳደብና ለአንባ ጓሮ ከመጋበዝ በስተቀር አንድም ቀን ከስሙ በፊት በሚጠራበት ድቁና አንዳችም የክህነት አገልግሎት ሲሰጥ ታይቶም ሆነ ተደምጦ የማይታወቀው መንገሻ ተክሌ የተባለው ግለሰብ፣ ዲያቆን ተብሎ ለመጠራት የቻለበትን የክህነት ማዕረግ ከየት እንዳገኘው የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ ዲያቆን ነኝና፣ የካህናት ጉባኤ አባል ነኝ ባይ በማለት እንደውም ከካህናቱ ቀድሞ ለመታየት የሚዳዳው ነው። ይህንን ድርጊቱን ከአፉ፣ ለማረጋገጥ http://www.youtube.com/watch?v=gnLIKSGIqJs ይመልከቱ።
በUKም ሆነ በመላው ዓለም የምትገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በአሁኑ ወቅት የወያኔ የጎሳ አፓርታይድ አገዛዝ በየዕለቱ ሰብዓዊ መብቱን በመረገጥ ድምጹን አፍኖ ግፍ ለሚፈጽምበት የኢትዮጵያ ህዝብ ድምጽ በመሆን የሚጮሁትን የዲያስፖራ ታጋዮች ዝም ለማሰኘት ዕቅድ ነድፎ በመንቀሳቀስ በተለይ በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ወኪሎቹንና ሰላዮቹን አስርጎ በማስገባት በዲያስፖራው ውስጥ አሉ የተባሉ ሃገር ወዳዶችና የሰብዓዊ መብት ታጋይ ኢትዮጵያኖች እያደኑ የተለያየ ጥቃት እንዲደርስባቸው ማድረግ አንዱ ዘዴው በመሆኑ በዚህ እድሜውን ሙሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሲጮህና ሲከራከር በኖረ ታጋይ ወንድማችን በወንድሙ መኰንን ላይ ለማድረስ የሚቃጣው ጥቃት የዚሁ አካል መሆኑን በመገንዘብ እነዚህ ስደተኛ በመምሰል ከስደተኛው ህብረተስብ ጋር በመቀላቀል የወያኔ የጥቃት መሣሪያ ሆነው በመሰለፍ በቤተ ክርስቲያንም ሆነ በሌላ ተቋማት የተሰገሰጉ ቅጥረኛ ባንዳዎችን መንጥሮ በማውጣትና በማጋለጥ ለድምጽ አልባው ሕዝባችን ድምጽ ሆነው የኖሩ ጀግኖቻችንን ከነሱ የጥቃት በትር መጠበቅና መከላከል ይኖርብናል።
ኢትዮጵያ በክብርና በነጻነት ለዘላለም ትኑር!!
http://ecadforum.com/Amharic/archives/9750/
No comments:
Post a Comment