Wednesday, March 25, 2015

አንድ ከፍተኛ የሕወሓት ወታደራዊ ባለስልጣን አምቦ ላይ ተገደለ::





Minilik Salsawi ትላንትና ከምሽቱ 2 ሰአት ላይ በኦሮሚያ ክልል አምቦ አከባቢ አንድ ከፍተኛ የወያኔ 
ወታደራዊ ባለስልጣን መገደሉ ታወቀ::አምቦ በከፍተኛ የጸጥታ ቁጥጥር ስር መውደቋ ተረጋግጧል:
:በአከባቢው የመብራት እና የስልክ አገልጎት ተቋርጦ ያደረ ሲሆን ይህንን የአከባቢው ነዋሪዎች ለሰይፈ 
ነበልባል ራዲዮ ጣቢያ ጋዜጠኛ እዮብ ባይሳ በሰጡት ቃለመጠይቅ አረጋግጠዋል::
በቀበሌ 2 በተባለ አከባቢ ሲያልፍ የነበረውንየወያኔ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣን የገደለው ማንነቱ ያልታወቀ
 ሲሆን አምቦ በከፍተኛ የደህንነት ቁጥጥር ስር ነች ያሉት ነዋሪዎቹ በጊዜው ጉዳዩን ያልተረዱና ከፍተኛ 
መደናገጥ እንደደረሰባቸው የተናገሩ ሲሆን ፖሊሶች እና ማንነታቸው የማይታወቁ የጸጥታ ሃይሎች ነዋሪዎችን እያስቆሙ 
እና እየፈተሹ እንደነበር ታውቋል::
ከአስረ አንድ ወራት በፊት ወያኔ የነደፈውን እና ገበሬዎችን የሚያፈናቅለውን የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን 
በመቃወም ከ27 00 በላይ የአምቦ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ ወተው የነበረ መሆኑ ሲታወስ የሕወሓት አግአዚ
 ሰራዊት ከ30 በላይ ያልታጠቁ ተማሪዎችን እና ነዋሪዎችን የገደለ እና የቤተሰባቸውን ደህንነት ለማረጋገጥ
 በቦታው የነበሩ ዜጎች ሳይቀር ለሞት እና ለቁስለት መዳረጋቸው የታወቀ ሲሆን የዘጠኝ አመት ሕጻን ታዳጊ
 ሳይቀር በሕወሓቶች መገደሉ ይታወሳል : ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

No comments:

Post a Comment