Thursday, February 27, 2014

ካሁን በኋላ “ወደ ቃሊቲ የምትገባው ታስረህ ካልሆነ በቀር እነ አንዱኣለምን ለማየት ድርስ አትላትም!”

አዲስ አበባ ነበርኩ። ሰኞ ጧት ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ርእዮት አለሙ ለመጠየቅ ቃሊቲ ማረምያቤት ሄድኩኝ። ጥበቃዎቹ ወደ ማረምያቤቱ አስተዳዳሪ ወሰዱኝ። አስተዳዳሪው ምርመራ ይሁን ዛቻ በማይታወቅ መልኩ ካስፈራራኝና ከሰደበኝ በኋላ ከማረምያ ቤቱ ተባረርኩ። አስተዳዳሪው “አንተ ከትግራይ አክራሪ አማራዎችን ለመጠየቅ ስትመጣ አታፍርም?!” አለኝ። ከፈለኩ ብሄር ብመጣም የፈለኩትን ሰው የመጠየቅ መብት አለኝ። የታሰረ ሰው መጠየቅ አያሳፍርም” መለስኩለት። ካሁን በኋላ “ወደ ቃሊቲ የምትገባው ታስረህ ካልሆነ በቀር እነ አንዱኣለምን ለማየት ድርስ አትላትም!” ብሎ ፖሊሶችን እንዲያስወጡኝ አዘዘ።
ወደ ቂሊንጦ ማረምያ ቤት ተጓዝኩ፤ ኡስታዝ አቡበክር አህመድን ለመጠየቅ። “አሸባሪ ለመጠየቅ መጣ” ተብዬ ለሦስት ሰዓታት ታሰርኩ። የቂሊንጦ ማረምያቤት ዋና አስተዳዳሪ እምባዬ ህቡዕ “አሸባሪዎችን ለማበረታታት መጣህ፣ ማረምያቤቱን ለመበጥበጥ ነው የመጣኸው። እንዳውም አሁን በማረምያቤቱ ረብሻ ተነስቷል። ስለዚህ ይታሰር” ብሎ በማዘዙ ወህኒቤት ዉስጥ ቆየሁ።
ዝርዝር ጉዳዩን ለመፃፍ እሞክራለሁ። አንዱኣለም አራጌና ርእዮት አለሙን አላየኋቸውም። አቡበክር አህመድ (ና ሌሎች ጉደኞቹ) ግን አግኝቻቸዋለሁኝ። እነ አቡበክር አህመድን በማግኘቴ ደስ ብሎኛል።

No comments:

Post a Comment