Friday, November 21, 2014

ከ400 በላይ ህዝብ የተፈናቀለበት መሬት በሙስና ተቸበቸበ

November 21,2014
በደቡብ ወሎ ዞን በኮምቦልቻ ወረዳ ቀበሌ 11 በተለምዶ ጋሪሳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ይኖሩ የነበሩ 470 ሰዎች ቦታው ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል ተብሎ ሰብአዊ መብታቸው ተጥሶ እንዲፈናቀሉ ከተደረገ በሁዋላ፣ በካሬ ሜትር 1 ብር ከ46 ሳንቲም መሬታቸው እንዲጨጥ ተደርጓል።
ጉዳዩ የህዝብ መነጋገሪያ ሆኖ ከቆየ በሁዋላ ሰሞኑን ከህዝቡ እየጨመረ የመጣውን ግፊት ተከትሎ በተደረገ ህዝባዊ ስብሰባና የካቢኔ አባላት ስብሰባ፣ የወረዳው አዛዦች ከተፈናቃዩ ደሃ ህዝብ የወሰዱትን መሬት በሙስና መቸብቸባቸውን እርስ በርስ እየተገላለጡ ይፋ አድርገዋል።
የወረዳው ላይዘን ኦፊሰር አቶ ሃብቶም የተባሉ ግለሰብ፣ አስተዳዳሪውን አቶ አበራ አበረን በአዲስ አበባና በባህርዳር መሬት ገዝተው ቤት መስራታቸውንና ቡልዶዘሮችን ገዝተው እያከራዩ መሆኑን ሲያጋልጡ፣ ምክትል ከንቲባው ደግሞ በባንክ ሂሳባቸው 8 ሚሊዮን ብር እንደተገኘባቸው እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች ቤቶችን መገንባታቸውን አጋልጠዋል። አጋላጩ አቶ ሀብቶምም በከተማዋ ሁለት ቦታ ገዝተው ቤት መስራታቸውን መቀሌ ላይ ተጨማሪ ቦታ መግዛታቸው በሌሎች ባልደረቦቻቸው ተጋልጧል።
ሶስቱም ባለስልጣኖች ለጊዜው ከስራቸው ቢታገዱም እስካሁን የተወሰደባቸው እርምጃ የለም። አንዳንድ ተፈናቃይ አርሶደአሮች ለኢሳት እንደገለጹት አቤቱታ ቢያቀርቡም ሰሚ በማጣታቸው ለስደትና ለረሃብ መዳረጋቸውን ለኢሳት ገልጸዋል ። ሰዎቹ ከስራ ቢሰናበቱም ወደ ሌላ ቦታ ተዛውረው መስራታቸው አይቀርም ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በደቡብ ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ ከ100 በላይ አርሶደሮች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። አርሶ አደሮቹ የመሬት ዋስትና ወረቀት እንዲሰጣችሁ በነፍስ ወከፍ 4 ሺ 500 ብር ክፈሉ ተብለው የተጠየቁ ቢሆንም፣ አርሶአደሮች ግን እስከዛሬ ግብር እየከፈልን ኖረናል፣ አሁን ተጨማሪ አንከፍልም በማለት ተቃውመዋል። ይህ ተከትሎ መሬታቸውን እየተቀሙ መሬቱ ለኢንቨስተር እየተባለ እየተቸበቸበ ነው።
አብዛኞቹ ባለስልጣኖች ከኢንቨስተሮች ጋር አክሲዎን እንዳላቸው መንጮች ለኢሳት ገልጸዋል። በአካባቢው የሚታየው ተደጋጋሚ ግጭት ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ።
ምንጭ  ኢሳት ዜና

ሰበር ዜና የአ.አ አስተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

 ‹‹ማስጠንቀቂያውን እንደ ቁም ነገር አንቆጥረውም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

• ‹‹ስርዓቱ ምን ያህል ዝቅጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል›› አቶ ግርማ በቀለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ሰማያዊ ፓርቲ ያስተባበረው የ9ኙ ፓርቲዎች የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ፀረ ህገ መንግስት በመሆኑና ነዋሪዎችን ሰላምና ፀጥታ በማወኩ በቀጣይ ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ካደረገ ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አስጠነቀቀ፡፡

አስተዳደሩ ትናንት ህዳር 11/2007 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ፤ ህዳር 6 ቀን ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ለህዝብ የተሰራጨው በራሪ ወረቀት ህገ ወጥ መሆኑን፣ ህዳር 7/2007 ዓ.ም በኢንጅነር ይልቃል ጌትነት መሪነት ሊደረግ የነበረው አደባባይ ስብሰባ ህገ ወጥ እንደነበርና በወቅቱ የስብሰባው ተሳታፊዎች ከፖሊስ ጋር ግብ ግብ ከመግጠማቸውም በተጨማሪ የአካባቢውን ህዝብ ሰላምና ፀጥታ አውከዋል ሲል ከሷል፡፡ አስተዳደሩ አክሎም ፓርቲው የአደባባይ ብጥብጥና ሁከት በመፍጠሩ እርምጃ እወስዳሉ ሲል ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ልኳል፡፡

በሌላ በኩል ሰማያዊ ፓርቲ በቀን 5/3/2007 ዓ.ም ለአስተዳደሩ የእውቅና ደብዳቤ ያስገባ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ አመራሮች አስተዳደሩ የላከው ደብዳቤ ከገዥው ፓርቲ ፍርሃት የመነጨ በመሆኑ ከእንቅስቃሴያቸው እንደማይገታቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብርና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ደብዳቤው ስርዓቱ የደረሰበትን መጠነ ሰፊ የፍርሃት ደረጃና ትግሉን ይበልጥ አጠናክረን መቀጠል እንዳለብን የሚያሳይ ነው ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ማስጠንቀቂው የደረሰው ሰማያዊ ፓርቲና የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹የረዥም ጊዜ የመንግስት ታሪክ ባላት አገር የከተማ አስተዳደር ነኝ ያለ አካል እንዲህ አይነት ደብዳቤ መጻፉ ኢትዮጵያ ምን ያህል ውድቀት እንደገጠማትና እኛም እንደ ህዝብ የውረደት ካባ መከናነባችን በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡ እንደ ሰማያዊ አሊያም የትብብሩ ሊቀመንበርነት ሳይሆን እንደ አንድ ይህን ያህል ውርደት እንደገጠማት አገር ዜጋ ሀፍረት ይሰማኛል፡፡›› ሲሉ አስተዳደሩ የላከው ደብዳቤ ላይ አስተያየታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ማስጠንቀቂያው በቀጣይ የፓርቲውም ሆነ የትብብሩ እንቅስቃሴ ላይ የሚያመጣው ችግር ካለ በሚል ለኢንጅነር ይልቃል ላነሳነላቸው ጥያቄም ‹‹ደብዳቤው የኢህአዴግ ፍርሃት ገደብ መልቀቁንና ትግሉም ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት የሚያሳይ ነው፡፡ ኢህአዴግ ሰላማዊ ህዝባዊ እንቅስቃሴን ብቻ ሳይሆን የራሱን ጥላም አለማመን ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳያል፡፡ እኛ ይህን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደቁም ነገር አንቆጥረውም፡፡ ይበልጡንም ለትግሉ በተጠናከረ መንገድ ንድንነሳሳ ይገፋፋናል›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ የትብብሩ ፀኃፊና የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ግርማ በቀለ ‹‹ማስጠንቀቂያው ትብብሩ በየሳምንቱ ያቀዳቸውን መርሃ ግብሮች ለማደናቀፍ ያለመ ነው፡፡ ከአንድ የመንግስት መስሪያ ቤት እንዲህ አይነት አሳፋሪ ደብዳቤ መጻፉ ስርዓቱ ምን ያህል ዝግጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል፡፡ ሆኖም ማስጠንቀቂያው ከእንቅስቃሴያችን አይገታንም፡፡ እንዲያውም ለዚህ የስርዓቱ ዝቅጠት የሚመጥን ስልት ነድፈን በጋራ እንድንሰራ ያደርገናል፡፡›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡



Thursday, November 20, 2014

የባዮሎጂ ምሩቁ ዶክተር ቴድሮስ አድሓኖም ለሕክምናው ሞያ ያለውን ባይተዋርነትና ንቀት በድጋሚ አረጋገጠ!

ዶ/ር ቴድሮስ ከአንድ አለማቀፍ የሚድያ ተቋም ጋር አደረገው በተባለው ቃለ መጠይቅ “ኢቦላ ኢትዮጵያ ውስጥ ቢገባ በቀላሉ ቁጥር ላይ እናውለዋለን፤ ምክንያቱም በደምብ የተደራጀ የጤና ልማት ሰራዊትና የኤክስቴንሽን ፓኬጅ አሰራር ስላለን” ማለቱን ተነግሯል፡፡
እግዚሀር ይይላችሁ፡፡ ዐለምን ሁሉ ያስጨነቀው ኢቦላ በጤና ኤክስተንሽን ሰራተኞች ሊቆጣጠር!
ዶ/ር ቴድሮስ የባዮሎጂና የፐብሊክ ሀልዝ ባለሙያ በመሆኑ ማስመሰልና ደፍረት እንጂ ይህ ነው የሚባል የሕክምና እውቀት ያለው ሰው ሆኖ አያውቅም፡፡ በሀገሪቱ ያለውን የሕክምና ትምህርት ጥራት እንዲሞት ቀጥተኛ ተሳትፎ ሲያደርግ የነበረና በኢትዮጵያ ሐኪሞች ዘንድ እጅግ የሚወቀስ አስመሳይ ሰው ነው፡፡
ዶ/ር ቴድሮስ ፓርላማ ላይ ቀርቦ “የሕክምና ሙያን ለማስተንፈስ “flooding “ የሚባል ፕሪንሲፕል እንጠቀማለን፡፡ ይኸውም በመላው ሀገሪቱ ባሉ የኒቨርሲቲዎች እስከ 9000 የሕክምና ተማሪዎች እንዲቀበሉ በማስገደድ ትምህርት አገኙ አላገኙ ብቻ ዶክተር አድርገን እናስመርቃቸዋለን” ብሎ የሚናገር ሰው ነው፡፡ በውጤቱም ይኸው በነርሶች የሚማሩ ሐኪሞች እየተፈበረኩልን ነው፡፡ ለዚህ ዐይነተኛ አብነት ዐዲግራት ዩኒቨርሲቲ ላይ ሶስተኛ ዐመቱ የያዘ የሕክምና ስልጠና ሲሆን አስተማሪዎቹም ሆነ የዲፓርትመንት ሓላፊ ኣዳዲስ ምሩቃን ነርሶች ናቸው፡፡ በዐለም ለመጀመርያ ጊዜ በነርሶች የሚማሩ ዶክተሮች የሚመረቱባት ሀገር- ኢትየጵያ፡፡
ቀጥሎ ደግሞ በዚች ሀገር የጤናው ዘርፍ ቀጥተኛና ከባድ ጉዳት ያደረሰውና እስከቅርብ ጊዜ የቀጠለው የተፋጠነ የጤና መኮንንነት (accelerated health officer ) ስልጠና ነው፡፡ ይኸው በዋናነት የፓርቲው ታማኝ ሰዎች በአንድ ዐመት ተኩል ስልጠና Health officer ተብለው የሚመረቁበትና ብዙዎቹም የሆስፒታሎች ስራ አስኪያጆች ሆነው የሚሾሙበት አሰራር ነው፡፡ መቸም ሳይማር ወረቀት ያገኘ ሰው የመማርና የልፋት ትርጉም አያውቅምና እነዚህ ሰዎች የከፍተኛ ባለሙያዎች ፀር በመሆን ተወዳዳሪ የሌላቸውና የሕክምና አሰጣጡን በከፍተኛ ደረጃ የጎዱ ናቸው፡፡
በርካታ ተመሳሳይ አብነቶች መጥራት ይቻላል፡፡
የዝቅጠቱና የድፍረቱ ቀጣይ ክፍል ደግሞ “ኢቦላን በጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች እንቆጣጠረዋለን” የሚል እጅግ አሳፋሪ ንግግር ነው፡፡
ከአስረኛ ክፍል ወድቀው የስድስት ወር ትንሽ ስልጠና ያገኙ ክትባት ከመስጠት ውጪ ስለሕክምና ምንም ነገር ያልሰለጠኑ፣ ምንም የማያውቁ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች እንዴት ይህንን ዐለምን ያስጨነቀና መድሓኒት ያልተገኘለት ቀሳፊ በሽታ “ይቆጣሩታል” ተብሎ ሰው ፊት ይወራል? ሲቀጥልም “ባለፉት ስድስት ዐመታት ጠንካራ የprimary health care ሲስተም ተሰርቷል” ይላል፡፡ እሱ የራሱን ስራ እና እያዋደደ ያለው፡፡በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስ፡፡
የትኛውም የሕክምና ባለሙያ በተለይም ሓኪም አሁን ያለው የታይታ የጤና ፖሊሲና አሰራር እጅግ የሾቀ እንደሆነና ለስራ እንቅፋት እንደሆነ ይነግራችኃል፡፡ የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ግን ለልፋታቸው ክብር የሚገባቸው ቢሆኑም እውነታው እንኳን ኢቦላ ወባና የሳምባ ምች የሚያክሙበት በቂ ስልጠና የላቸውም፡፡ አሁን እንደአዲስ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስፋፋ ያለው የmeasles በሽታም በዋናነት ክትባቶቹን በስነ-ስርዐት ባለመያዝ (cold chain ባለመጠበቅ)ና፣ በተገቢው ባለመስጠታቸው ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚጠየቁበት እነሱ ሳይሆኑ በቂ ስልጠናና እውቀት ያላስጨበጣቸው አካል ነው፡፡ እነሱ በትንሽ ገንዘብ ታች ወርደው እየሰሩና መከራቸውን እየበሉ ያሉ ናቸው፡ ቢሆንም ግን ከመነሻውም በዋናነት ለፕሮፖጋንዳ ታስቦ የተሰራ ነውና ምንም ተጨባጭ መሰረታዊ ስልጠናና እውቀት አንዲጨብጡ አይደረጉም፡፡
ያም ሆነ ይህ ያለሙያውና ከንቀት የመነጨ አባባሉ እጅግ የሚያስቆጣ የድፍረትና የድንቁርና ንግግር ነውና እናወግዘዋለን፡፡ ኢቦላ እንዳይገባ መከላከልና መከልከል እንጂ ሌላ አማራጭ የለም፡፡ እንኳን እኛን በደምብ የተደራጀ የጤና መሰረተ-ልማትና ቅንጅታዊ አሰራር ያለው የዳበረ የጤና ሲስተም ያላቸውን አውሮፓንና አሜሪካን እንኳ ከፍተኛ ስጋት የደቀነባቸው ከባድ አደጋ ነው፡፡ በሆነ ምክንያት ሀገራችን ቢገባ ግን በዚህ የሾቀ የጤና መሰረተ-ልማትና የወረደ የጤና ፖሊሲ ቅንጅት ለመቆጣጠር የሚታሰብ አይደለም፡፡ ድንቁርና ወለድ ድፍረት ቢቀርብንስ?
ኢቦላ እንዳይገባብን መከላከል ነው ብቸኛው አማራጭ-ጃል፡፡

Tuesday, November 18, 2014

በኦሮምያ ዜጎችን ማሰሩ እንደቀጠለ ነው

ኀዳር ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ የሚታሰሩ ዜጎች ቁጥር መበራከት የአለምን የመገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ባገኘ ማግስት፣ አሁንም ዜጎችን በሰበብ አስባቡ እያሰሩ ለፍርድ አቅርቦ ማስፈረድ ቀጥሎአል።
አፍሪካ ቀንድ የሰብአዊ መብት ሊግ ያወጠው ሪፖርት እንደሚያሳየው ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በአምቦ ከተማ እና በሚዳ ቀኒ ወረዳ ከ20 ያላነሱ ተማሪዎች፣ መምህራንና አርሶ አደሮች ታስረዋል። እስራቱ የተፈጸመው መንግስት የአካባቢውን መሬት ለኢንቨስተሮች መስጠቱን ተከትሎ በተነሳ ተቃውሞ ነው። ከታሰሩት መካከል
አርሶ አደር ኪጣጣ ረጋሳ፣ ተማሪ ቶሎሳ ተሾመ፣ ድሬ ማሾ፣ ታሪኩ ቡልሾ፣ ያለው ባንቲ፣ ቢንያሳ ኢባ፣ ተስፋይ ቢይነሳ እና ነጋዴ መግስቱ ሞሲሳ ይገኙበታል።
እንዲሁም ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የጅምላ እስራቶች እየተከናወነ ነው። ብዙዎቹ በህጋዊ መንገድ የሚታገለው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባላት በመሆናቸው ብቻ መታሰራቸውን የሚገልጸው ሊጉ፣ በጅማ የድርጅቱ አመራሮች የሆኑት አቶ አጀብ ሼክ ሙሃመድ፣ አቶ ሙሃመድ
አሚን ካልፋና አቶ ነቢብ ጀማል ታስረው 2 አመት ከስድስት ወር እንደተፈረደባቸው ጠቅሷል።
ተፈጸመ ስለተባለው እስራት ያነጋገርናቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ተጠሪ አቶ በቀለ ነገአ ሰዎቹ በሃሰት እንደተፈረደባቸው አረጋግጠዋል። መሳሪያ የሌላቸውን ህገወጥ መሳሪያ ደብቃችሁዋል በሚል በሃሰት ተመስክሮባቸው መታሰራቸውን አቶ በቀለ አስረድተዋል ከታሳሪዎች መካከል የአቶ አጀብ ሼክ ሙሃመድ
ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ አዳነች ለኢሳት እንደገለጹት ደግሞ ባለቤታቸው በሀሰት ተመስክሮባቸው ከታሰሩ ጀምሮ እርሳቸውም በሚደርስባቸው ማስፈራሪያ ከቤት ለመውጣት መቸገራቸውን ገልዋል። ወደ ጎረቤት ሄደው እሳት እንዳይጭሩ ከመከልከላቸውም ሌላ፣ ቤታቸው በደንጋይ የደበደባል። የባለቤታቸው ወንድም ተመሳሳይ ችግር ስላጋጠመው ስራውን ትቶ ወደ ከተማ መምጣቱንም ወ/ሮ አዳነች ተናግረዋል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሰሞኑን እስር ቤቶች በኦሮሞ ተወላጆች መሞላቱን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ አለም የመገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ሰጥተውታል።

አምባገነንነት ከምድረገፅ መጥፋት አለበት!

ባለፈው ሳምንት ቡርኪናፋሶን ለ27 ዓመታት እንደ ግል ንብረታቸው ሲያዙባት የከረሙት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ብሌስ ኮምፓዎሬ፤ የሥልጣን ዘመናቸውን ለማራዘም ሲሉ ህገመንግስቱን ለማሻሻል ያደረጉት (ንቀትና ድፍረት የተቀላቀለበት ነው) ሙከራ ያስከተለው ውጤት ያልጠበቁት ነበር፡፡ (አመዳቸውን ቡን ሳይል አልቀረም!) ምንም ቢሆን የህዝብ አመፅ አይጠብቁማ፡፡ መቼም የሥልጣን እህል ውሃቸው ቢያልቅ ነው እንጂ አምባገነኖች እንዲህ በቀላሉ ከቤተመንግስት እኮ አይወጡም፡፡ (ያውም በአንዲት ቀን አብዮት?!) አመጽና ተቃውሞን በሃይል ለመመከትና ለማፈን ሁሌም ታማኝና አስተማማኝ ወታደራዊ ኃይል ከጎናቸው አይጠፋም፡፡ የስልጣን ገመዳቸው ተበጠስ ያለው ጊዜ ግን ወታደሩም ፊቱን ያዞርባቸዋል፡፡ በአምባገነኖቹ የአፍሪካ መሪዎች በእነ ጋዳፊ፣ ሁስኒ ሙባረክ…አይተነዋል፡፡
የአምባገነን መሪዎችን ባህሪና ነገረ ስራ እንደ አዲስ ለመፈተሽ ያነሳሱኝ (Inspiration ሆነውኛል!) ከስልጣን ከተወገዱ የሳምንት ዕድሜ ብቻ ያስቆጠሩት የቡርኪናፋሶው የቀድሞ መሪ ናቸውና ምስጋና ይገባቸዋል (አምባገነን ማመስገን ነውር ነው እንዳትሉኝ!) እናላችሁ ፍተሻዬን ውጤታማ ለማድረግ በአምባገነን መሪዎች ዙሪያ ያልበረበርኩት መረጃ የለም፡፡ (ዕድሜ ለእነ ጐጉል!) የእያንዳንዱን አምባገነን ታሪክ (ሥልጣን ከተቆናጠጠበት እስከተገረሰሰበት) በሰከንዶች ቅጽበት ማግኘት ይቻላል፡፡ ዲሞክራሲያዊ መብቶች ባልተከበሩበት አገር፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሊስፋፋ እንደማይችል ልብ ይሏል፡፡ (ነፃነት ሳይኖር ፈጠራ እሺ አይልም!) በነገራችሁ ላይ “ስኬታማ አምባገነን የመሆን ምስጢር” በሚል ርዕስ በታተመ መጽሐፍ ላይ እንዳነበብኩት፤ አምባገነን መሪዎች በአገር ስም ብዙ ገንዘብ እየተበደሩ፣ ቀጣዩን ትውልድ ለዕዳ በመዳረግ ዝነኛ ሲሆኑ መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ደሞ ዳተኞች ናቸው፡፡ አቅም በማጣት ብቻ እንዳይመስላችሁ፡፡ አንዳንዴ ሆን ብለው ነው፡፡ መንገድ ከተስፋፋ የሚቀናቀናቸው የፖለቲካ ቡድን ከሸመቀበት ወጥቶ ቤተመንግስት ድረስ ዘው እንዳይል ክፉኛ ይሰጋሉ፡፡ (የስልጣን አወጣጣቸውን ያውቁታላ!!)
እናላችሁ… ዛሬ የጥቂት አምባገነን መሪዎችን እንግዳ ባህርያት አብረን እየቃኘን እንደመም፡፡ እናንተ…ሥልጣን እንዲህ ያሳብዳል? ሥልጣን እንዲህ ያቃዣል? ሥልጣን እንዲህ ያስዋሻል? ሥልጣን እንዲህ ያስቀላምዳል? በሉ አብረን “አጃኢብ” እንበል፡፡
ራሳቸውን “የዕድሜ ልክ ፕሬዚዳንት” ብለው በመሰየም የሚታወቁት የሃይቲው የቀድሞ አምባገን መሪ (እ.ኤ.አ ከ1907-1971 ገዝተዋል) ፍራንሶይስ ዱቫሊየር፤ ለ14 ዓመት የዘለቀው የስልጣን ዘመናቸው በጥርጣሬና በፍርሃት የተሞላ ነበር፡፡ (ሥራቸው እኮ ነው የሚያስፈራቸው!?) በነገራችሁ ላይ በየትኛውም የዓለም ክፍል የነበሩና ያሉ አምባገነኖች በአብዛኛው ይመሳሰላሉ (ለእነሱ “የእናት ሆድ ዥንጉርጉር” አይሰራም!) እናላችሁ… የሃይቲው አምባገነንም ቢፈሩና ቢጠራጠሩ አይፈረድባቸውም፡፡ አንደኛ የፈፀሙትን ግፍና ጭካኔ ያውቁታል፡፡ ሁለተኛ ሥልጣን አንዴ ከእጅ ከወጣ አይመለስም፡፡
ዱቫሊየር ለስልጣናቸው ስጋት የመሰሏቸውን ሁሉ አንድ በአንድ አስወግደዋል፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን (ቦይ ስካውቶችን ሳይቀር) ያገዱ ጠርጣራ መሪ ነበሩ፡፡ ባዕድ አምልኮ የተጠናወታቸው የሃይቲው የቀድሞ መሪ፤ ወር በገባ በ22ኛው ቀን የሚጠብቀኝ መንፈሳዊ ኃይል አለ ብለው ያምኑ እንደነበር ይነገራል፡፡ በስልጣን ዘመናቸው የመጨረሻ ዓመታትም ወር በገባ በ22ኛው ቀን ብቻ ነበር ከቤተመንግስት የሚወጡት፡፡ (ስልጣን ሊያልቅ ሲል ያሳሳል!)
አንዴ የሃይቲ የፓርላማ ቡድን መሪ የነበሩ ክሊመንት ባርቦት የተባሉ የፖለቲካ ተቀናቃኛቸው፤ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድርገውባቸው ተሰውረው ነበር፡፡ ፕሬዚዳንቱ እኚህ “ህገመንግስት በሃይል ለመናድ” የሞከሩ ተቀናቃኝ፤ ከተሸሸጉበት ተይዘው እንዲመጡላቸው ለፖሊስ ትዕዛዝ ያስተላልፋሉ፡፡ ሆኖም ፖሊስ “አስሼ አስሼ አጣኋቸው” ይላቸዋል፡፡ ይሄኔ ዱቫሊየ ምን ቢሉ ጥሩ ነው? “ባርቦት ራሱን ወደ ጥቁር ውሻ ቀይሮ ነው” አሉና አረፉት፡፡ ከዚያም በሃይቲ የሚገኙ ጥቁር ውሻዎች በሙሉ እንዲገደሉ አዘዙ (የሃይቲ ውሾች ሳይቀሩ የአምባገነን ሰለባ ሆኑ!) የማታ ማታ ግን የተሰወሩት ባርቦት ተገኙ፡፡ እሳቸውንም አልማሯቸውም፡፡ የሞት ቅጣት ፈረዱባቸው፡፡ ጭንቅላታቸውን ቆርጠውም ለሚያምኑበት ባዕድ መንፈስ እንዳስቀመጡለት ይነገራል፡፡
አንድ ጊዜ ምን እንደታያቸው አይታወቅም፡፡ ምርጫ ይካሄድ አሉ – ነፃ ምርጫ፡፡ 100 ፐርሰንት ድምፅ አግኝተው አሸነፉ (ድንቄም ነፃ ምርጫ!) በነገራችሁ ላይ እኚህ አምባገነን መሪ ስድስት የግድያ ሙከራዎችን (በራሳቸው ጥበብ ይሁን በባዕድ መንፈስ ኃይል አልታወቀም!) …አምልጠዋል፡፡ በመጨረሻም የተወሰነ ጊዜ ታመው እ.ኤ.አ በ1971 ዓ.ም ሞቱ፡፡ ህዝቡ እሳቸውን ቢገላገልም የሥልጣን መንበሩን የተረከበው ልጃቸው ነበር፡፡
ወደ አፍሪካ ስንመጣ የቀድሞውን የኡጋንዳ አምባገነን መሪ ኢዲ አሚንን (ከ1920-2003) እናገኛለን፡፡ እኚህን አምባገን ሳስባቸው የስፔናዊው ደራሲ ሴርቫንቴ “ዶን ኪሆቴ” መፅሃፍ ላይ ያለው ዋና ዶን ኪኾቴ የተባለ ገፀ ባህርይ ትዝ ይለኛል (አወይ መመሳሰል አሉ!) ራሳቸውን “የህይወት ዘመን ፕሬዚዳንት”፣ “የታላቋ ብሪታኒያ ግዛት አስገባሪ”፣ “የስኮትላንድ የመጨረሻው ንጉስ” እያሉ የሚጠሩት ኢዲ አሚን፤ ፊልድ ማርሻል የተባለውን የመጨረሻ ከፍተኛ ወታደራዊ ማዕረግ ለራሳቸው የሸለሙ ዕብሪተኛ መሪ ነበሩ፡፡
የኢዲ አሚን አስገራሚና ቅጥ አምባሩ የጠፋ ባህርይ ተዘርዝሮ አያልቅም፡፡ የአንድ ታዋቂና ሃብታም እስያዊ ቤተሰብ ልጅ የሆነች ኮረዳን ለትዳር ጠይቀው አዎንታዊ ምላሽ ያላገኙት አሚን፤ የአፀፋ እርምጃቸው አስደንጋጭ ነበር፡፡ በኡጋንዳ የሚኖሩ እስያዊያንን በሙሉ ከአገሪቱ አባረሩ፡፡ (እብሪት ነው እብደት?) የአፍሪካ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የሰሩት አስገራሚ ድራማም ተጠቃሽ ነው፡፡ ወደ ስብሰባው አዳራሽ የገቡት ዙፋን በሚመስል ወንበር ላይ ተቀምጠውና አራት ነጮች ከእነ ወንበራቸው ተሸክመዋቸው ነበር፡፡ የዚህን ምክንያት በአግራሞት ለተሞሉት የአፍሪካ ሚኒስትሮች ሲያስረዱም፤ “እኛ አፍሪካውያን አውሮፓውያንን ስንሸከም ኖረናል፡፡ አሁን ደግሞ የሚሸከሙን እነሱ ናቸው፡፡ እኛ አሁን ጌታ መሆናችንን ለማሳየት ብዬ ነው” አሉ – ሞኝ ይሁኑ ብልህ የማይታወቁት አሚን፡፡ ኢዲ አሚን ይሄ ተግባራቸው እንዳሰቡት አድናቆትን አላተረፈላቸውም፡፡ እንደውም በአፍሪካ መሪዎች ዘንድ ክፉኛ አስተችቷቸዋል (ሌሎቹም ከእሳቸው ብዙ ባይለዩም!)
ኢዲ አሚን፤ ዋና ፉክክራቸው ከእንግሊዟ ንግስት ኤልዛቤት ጋር ነበር (ንግስቲቷ ነገሬ ባትላቸውም!) እናም አንድ ጊዜ “የጋራ ገበያ አገራት ሊቀመንበር መሆን ያለብኝ እኔ እንጂ ንግስቲቷ አይደለችም” ሲሉ በድፍረት ተናግረው ነበር (አምባገነንነት ላይ እብደት ሲታከልበት ውጤቱን አስቡት!) እኔ መቼም ሰውየው “አምባገነን ነበሩ” በሚል ብቻ አላልፋቸውም፡፡ እንዴ ከዚህ የበለጠ እበደት አለ እንዴ? በነገራችሁ ላይ አሚን…ለንግስት ኤልዛቤት በርካታ የፍቅር ደብዳቤዎችን እንደፃፉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ (ንግስቲቱ ምን ብለው ይሆን?)
አምባገነኑ መሪ፤  ዋና ዋና የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸውን አድራሻ በማጥፋት የሚደርስባቸው አልነበረም፡፡ እንዴት? ለኢዲ አሚን ቀላል ነበር፡፡ ያስገድሏቸዋል፡፡ ይገድሏቸዋል፡፡ የእሳቸው ነገር በዚህ ብቻ አያበቃም፡፡ የሰው ስጋ ይበሉ ነበር ይባላል፡፡ ተቀናቃኞቻቸውን ካስገደሉ ወይም ከገደሉ በኋላ  አንድም ራሳቸው ይበሏቸዋል አሊያም ደሞ ለለማዳ አዞዎቻቸው ቀለብ ያደርጓቸዋል ይባል ነበር፡፡ ይሄ በሁነኛ ማስረጃ ባይረጋገጥም በአንድ ወቅት አማካሪያቸውን ከእራት በፊት ጠርተው፤ “ያንተን ልብ እፈልገዋለሁ፤ ልጆችህንም ልበላቸው እሻለሁ” በማለት ክው እንዳደረጉት ተዘግቧል፡፡
አሚን ከአምስት በላይ ሚስቶች የነበራቸው ሲሆን (በተመሳሳይ ጊዜ እኮ ነው!) ከእነዚህ ሚስቶቻቸውም ከደርዘን በላይ ልጆችን ወልደዋል፡፡ አሳዛኙ ነገር አንደኛዋ ሚስታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድላ ፍሪጅ ውስጥ መገኘቷ ነው፡፡ (የአምባገነንነት መጨረሻ ጭራቅነት ሳይሆን አይቀርም!!)
እ.ኤ.አ ከ1940-2006 ዓ.ም የቱርክሜኒስታን ፕሬዚዳንት የነበሩት ሳፓርሙራት ኒያዞቭ ደግሞ በህዝባቸው ውስጥ የራሳቸውን አምልኮተ-ስብዕና በመገንባት ወደርየለሽ ነበሩ፡፡ 15 ሜ. (50 ጫማ) ቁመት ያለው የወርቅ-ቅብ ሃውልታቸውን በቁማቸው ያሰሩ ዕብሪተኛ መሪ ናቸው፡፡ ሃውልታቸው ሁልጊዜ ፊቱ  ወደ ፀሐይ አቅጣጫ እንዲሆን ታስቦ የሚሽከረከር ሆኖ ነበር የተሰራው፡፡
ፎቶአቸውን በየግንቡና በየህንፃው ላይ ማየት የሚያስገርም አልነበረም፡፡ በአገሪቱ የገንዘብ ኖቶች ላይ ሳይቀር ምስላቸው ነበረ፡፡ አብዛኛው ህዝብ በድህነት ሲዳክር በነበረበት በዚያ ዘመን ኒያዞቭ፤ በበረሃነቷ በምትታወቀው ቱርክሜኒስታን እምብርት ላይ ግዙፍ የበረዶ ቤተመንግስት ያሳነፁ አምባገነን ነበሩ፡፡ (በነገራችሁ ላይ ሰሞኑን ቢቢሲ እንደዘገበው፤ የአሁኑ የቱርክ መሪ ከ600 ሚ.ዶላር በላይ አውጥተው ያሳነፁት ቤተመንግስት የህዝብ ተቃውሞ አስነስቷል!) አምባገነኖች አንድ ናቸው አልተባባልንም!
ሰውየው እልም ባለ በረሃ ላይ ሰው ሰራሽ ሃይቅ እንዲገነባላቸውም ትዕዛዝ ሰጥተው ነበር፤ ይሰራ አይሰራ ባይገለፅም፡፡ እኚህ አምባገነን እንደ ሌሎች አምባገነኖች ሁሉ ሥልጣን በያዙ ማግስት የመጀመሪያ ሥራቸው ያደረጉት የመንገዶችን፣ ህንፃዎችን፣ ከተሞችን፣ ፓርኮችን ወዘተ… ስያሜዎች መቀየር ነበር (አብዛኞቹን በራሳቸው ስም ሰይመዋቸዋል!) ይሄ ብዙም ላያስገርም ይችላል፡፡ (አምባገነን ሁሉ ያደርገዋላ!) በጣም  የሚገርመው ግን ምን መሰላችሁ? የዓመቱን ወራት… እነ ጃንዋሪ፣ ፌብሯሪን በራሳቸው፤ በቤተሰባቸውና በመጽሐፋቸው ስም መሰየማቸው ነው፡፡ (አጃኢብ እኮ ነው!) ሌላው ቀርቶ Bread ወይም “ዳቦ”ን እንኳን አልተውም፡፡ በእናታቸው ስም ሰይመውታል፡፡
አምባገነኑ የቱርክሜኒስታን የቀድሞ መሪ ይበልጥ የሚታወቁት ግን በደነገጓቸው አስገራሚ ህጐች ነው፡፡ በነገራችሁ ላይ እ.ኤ.አ በ1997 ዓ.ም ሲጋራ ማጨስ ማቆማቸውን ተከትሎ ሚኒስትሮቻቸው በሙሉ እንደሳቸው ማጨስ እንዲያቆሙ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጥተው ነበር፡፡ እንደ ሳዳም ሁሴንና ጋዳፊ ሁሉ እሳቸውም መፅሃፍ ፅፈዋል፡፡ (አምልኮተ – ስብዕና የመገንባት አባዜ እኮ ነው!)የመፅሃፉ ርዕስ “ሩክህናማ” ወይም “የነፍስ መፅሃፍ” የተሰኘ ሲሆን ትክክለኛውን መንገድ የሚያስተምርና ከአሉታዊ ተፅዕኖዎች የሚከላከል እንደሆነ ይነገርለት ነበር፡፡ የሚያስገርመው ታዲያ ምን መሰላችሁ? ይሄ መፅሃፍ በት/ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርት ሥርዓት ውስጥ እንዲካተት መደረጉ ነው፡፡ በዚህ ብቻ ግን አያበቃም፡፡ የመንግስት ሠራተኞች ከስራቸው እንዳይባረሩ ከፈለጉ መጽሐፉን በቃላቸው መሸምደድ ይጠበቅባቸው ነበር፡፡ ዜጐች የመንጃ ፈቃድ ሊያወጡ ሲሉ ዋናው መስፈርት የፕሬዚዳንቱን መጽሐፍ ከጫፍ እስከጫፍ እጥብ ማድረግ ነው፡፡ ከመጽሐፉ የወጡ ጥያቄዎችን በተገቢ ሁኔታ ያልመለሰ መንጃ ፈቃድ አይሰጠውም፡፡ (የአምባገነንነትን ጥግ አያችሁልኝ!) ፕሬዚዳንቱ የደነገጓቸውን ህጐች ረሳናቸው እኮ፡፡ ወንዶች ፀጉርና ፂም እንዳያስረዝሙ እገዳ ተጥሎባቸው ነበር፡፡ ለቲቪ ዜና አቅራቢዎች ሜክአፕና የወርቅ ጥርስ አይፈቀድም ይላል – ህጋቸው፡፡
አምባገነኑ የቱርክሜኒስታን የቀድሞ ፕሬዚዳንት የፈረስ አፍቃሪ ነበሩ፡፡ ይሄን ፍቅራቸውን ለመወጣትም በ20 ሚ.ዶላር የፈረስ መዝናኛ ማዕከል ያስገነቡ ሲሆን ማዕከሉ የመዋኛ ገንዳ፣ የአየር ማቀዝቀዣና የህክምና አገልግሎቶች የተሟሉለት ነበር፡፡ (ይሄ ሁሉ ድሆች በሞሉባት አገር እንደነበር አትዘንጉብኝ!) እኚህ አምባገነን መሪ ከስልጣን የወረዱት በ2006 ዓ.ም ሲሞቱ ነው፡፡ የወርቅ ቅብ ሃውልታቸው ደሞ ከአራት ዓመት በኋላ በ2010 ዓ.ም ከተተከለበት ስፍራ ተወግዷል (ደርግ ሲገረሰስ የተገነደሰው የሌኒን ሃውልት ትዝ አለኝ!) እሳቸውን የተኳቸው ፕሬዚዳንት ደግሞ የፈረስ የቁንጅና ውድድር በ2011 እንዳዘጋጁ ተዘግቧል  (ማለቂያ የሌለው የአምባገነኖች እብደት…አትሉም!)
እኔ ሳስበው ግን አምባገንነት የአገዛዝ ሥርዓት ወይም የግለሰቦች ባህርይ (ስብዕና) አይመስለኝም፡፡ እብደት ወይም ለእብደት አንድ ሃሙስ የቀረው የአዕምሮ መታወክ በሽታ ነው፡፡ ፍርሃት…ጥርጣሬ…ቅዠት…ጀብደኝነት…ጭካኔ…እብሪት…የበሽታው ምልክቶች ናቸው፡፡ የአምባገነንነትን ደዌ እንደ ፖሊዮ ከምድረገጽ ለማጥፋት ብዙ ትጋትና ጥረት ይጠይቃል፡፡ (ከአምባገነንነት የፀዳች ዓለም እኮ ገነት ናት!)

Monday, November 17, 2014

Intensifying Mass Arrest, Torture, and Killing will Only Inflame Struggle of for Freedom

Intensifying Mass Arrest, Torture, and Killing will Only Inflame Struggle of for Freedom

   
(Qeerroo):-It is to be recalled that tens of thousands of Oromo nationals in general and Oromo students in particular have been arrested and severely tortured by the TPLF-led Ethiopian regime over the last few months in connection to a series of Oromo student protests which broke out in large scale and spread out throughout Oromia beginning the month of April, 2014. These protests, organized and led by the National Youth Movement for Freedom and Democracy (aka Qeerroo Bilisummaa), are just one incident in a series of continued struggle of the Oromo nation for freedom, democracy, and justice over the last 23 or so years. Hundreds have been gunned down by live bullets by the so called Agazi troops of the regime in the months of April and May, 2014.

 In addition to those who have been shot and killed during the protests, many have lost their lives in prison cells unable to stand the brutal torture. Many others have simply disappeared. Qeerroo Bilisummaa believes that those who disappeared have been killed and their bodies hidden – a practice repeatedly perpetrated on the Oromo prisoners by this regime.
On July 7, 2014 Qeerroo Bilisummaa has compiled a list of 61 Oromos killed and 903 others rounded up and thrown into jail during the April/May Oromo student protests of universities, colleges, high schools, middle schools and other educational institutions. Our evidence indicates that all those who have been arrested have undergone through intense interrogation which involved severe and brutal torture. Many have lost their lives due to the severe torture. For example, a 2nd year Computer Science Oromo student of Haromaya University, Aslan (Nuradin) Hasan, was killed as a result of extended torture in prison on June 04, 2014. On the same day a 10th grade student, Dawit Wakjira, was arrested and beaten to death in Anfillo district, Qellem Wollega zone. 


Again on the same day a young high school teacher, Magarsa Abdissa, was beaten and killed in Gulliso Prison, West Wollega zone. The fact that these three young Oromos are known and reported to have been beaten to death on the same day, from different parts of Oromia, is a testimony that prisons in the empire are not safe places under this regime. It has to be noted that many other killings that occurred in the prison cells remained hidden as it is extremely difficult and risky to compile reports of such brutal killings under tight security machinery of the regime.
Number of Oromos ChargedThe arrests and tortures have continued non-stop. More and more are being arrested before those who are in jail are released or brought to court. Many of those who survived the torture will remain incarcerated, without any charge, until they confess the accusations brought against them. On many other prisoners, concocted charges and false witnesses have been prepared and they are brought to the kangaroo court of the regime to pass a long time sentence on them so as to legitimize their prison term. Everybody who pays close attention to how the judicial system of the regime operates knows for sure that the so called “court” of the regime is just a place where a fictitious drama is performed. Qeerroo Bilisummaa believes no justice is expected from the so called “court” of the current Ethiopian regime at any level.


In this brief statement the data collection team of Qeerroo Bilisummaa has compiled a list of 183 Oromos, from 6 different zones of Oromia, mainly students, on which the regime has finalized its trumped up charges in order to pass a “guilty” verdict on these young innocent Oromo students and others and sentence them to several years of prison. The main content of the charges brought against them is “having connection with the Oromo Liberation Front (OLF)” and “participating on the public protest against the government”. These Oromo students and other Oromo individuals are in addition to several hundreds of prisoners Qeerroo has reported in the last few months and our reports indicate that they are going under severe torture and they are denied food, health care, closing and basic needs to sustain their lives.


Qeerroo Bilisummaa strongly demands that the Ethiopian regime drop all charges against these Oromo nationals and tens of thousands others and release them immediately and unconditionally. We would like to reiterate that we the Oromo youth Qeerroo will not sit and be silent when part of our body is bleeding. The Ethiopian regime should realize that intensifying arrest, torture and killing will only inflame the struggle of the Oromo people for their right. More oppression doesn’t lead to submission. It rather breeds more dissenting voices. We are certain that eventually the Oromo and other oppressed nations and nationalities will bring down this criminal regime and justice and freedom will prevail. Read Full Statement:- Continued Arrest and Conviction of Oromo Students from Various Zones of Oromia

Source:- Qeerroo.org 

Sunday, November 16, 2014

አዲሱ የአምልኮ፣ አለባበስ እና አመጋገብ ስርዓት በአ. አ. ዩኒቨርሲቲ ከህዳር 30 ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ መመሪያ ተላለፈ

hijab addis ababa
አቡ ዳውድ ኡስማን
ትምህርትህ ሚኒስተር የዜጎችን ህገ መግስታዊ መብት በመጣስ አዲስ ባወጣው የአምልኮ፣ አለባበስ እና አመጋገብ ስርአት ደንብ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከህዳር 30 ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ትዕዛዝ ማስተላለፉን ምንጮች ዘግበዋል፡፡
በአዲሱ የትምህርት ሚኒስተር ደንብ መሰረት ማንም ሙስሊም ሃይማኖቱ የሚደነግግበትን ግዴታዎች መፈፀም የሚከለክል ሲሆን በተለይም ሙስሊም ሴት እህቶቻችን ሂጃባቸውን እንዲያወልቁ አልያ ደግሞ ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡ የሚያስገድድ ነው፡፡
ሴኩላሪዝም ሲባል መንግስት እና ሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸውን የሚገልፅ መርህ ቢሆንም ሴኩላር ሊሆን የሚችለው መንግስታዊ ስርአቱ እንጂ ሰዎቹ አለመሆናቸው ግልፅ ነው፡፡ ሆኖም ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከሃይማኖቱ ለማራቅ ከተነደፈው ዋነኛ ስትራቴጂ አንዱ በትምህርት ቤቶች እና በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም በመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ሙስሊሞች በሃይማኖታቸው ግዴታ የተደረገባቸውን ድንጋጌዎች እንዳይተገብሩ የሚያዝ መመሪያ ማውጣት አንዱ ነው ፡፡
ይህ ህገ ደንብ በረቂቅነት በወጣበት ጊዜ በወቅቱ በሙፍቲህ ሃጂ ኡመር ኢድሪስ በሊቀመንበርነት ይመራ የነበረው የኢትዬጲያ ኡለማዎች ምክር ቤት ህገ ደንቡ ከኢስላማዊ ድንጋጌዎች ጋር የሚጋጭ በመሆኑ ማስተካከያ እንዲደረግበት መጠየቃቸው የሚታወስ ቢሆንም በመንግስታዊ ተሷሚ መጅሊሶች እንዲጸድቅ መደረጉ ይታወቃል፡፡
ይህንንም ህገ ደንብ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተግባራዊ እያደረጉት ሲሆን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ከ ህዳር 30 ጀምሮ በሁሉም ካምፓስ የሚገኙ አስተዳደሮች እና የጥበቃ ሰራተኞች ህገ ደንቡ ተግባራዊ መሆኑን በጥብቅ እንዲከታተሉ ጥብቅ ማሳሰቢያ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ትዕዛዝ መውጣቱን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡
በመላው ሃገሪቱ ሙስሊም ሴት እህቶቻችን ሂጃባችሁን አውልቁ በሚል ከትምህርት ገበታቸው እየተፈናቀሉ እንደሚገኙ መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡