Thursday, October 16, 2014

በኢትዮጵያ ተከታታይ ፍንዳታዎች ይደርሳሉ የሚለው ስጋት አይሏል * ደህነቶች እና የኢምባሲ አታሼዎች(ተወካዬች) በስብሰባ ተወጥረዋል

በኤምባሲዎች የደህንነት አታቼዎች(ተወካዬች) እና በወያኔ የደህንነት ባለስልጣናት መካከል ስብሰባ እየተካሄደ ነው።

ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው 
በኢትዮጵያ ውስጥ ተቀማጭነታቸውን ያደረጉ ምእራባውያን ዲፕሎማቶች ዘንድ የሚደርሱ እናፈነዳለን መረጃዎች ከፍተኛ የሆነ ስጋት እየፈጠሩ መሆኑን በአዲስ አበባ የሚገኙ እና ለደህንነት አታቼዎች ቅርብ የሆኑ ምንጮች ገልጸዋል።

ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ሰዎች እንደሚናገሩት መሃል አገርን እና ምስራቅ ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪት ክልሎች ይደረጋሉ የተባሉ ፍንዳታዎች ከአልሸባብ የመጡ ማስጠንቀቂያዎች ናቸው ቢባልም በአልሸባብ ውስጥ በተደረገ የመረጃ ማጣራት አልሸባብ ይህንን መረጃ እንዳልበተነ በአዲስ አበባ የአሜሪካን የደህንነት አታቼ ለማረጋገጥ ያደረጉት ሙከራ በከፊል ባይሳካም የሁኔታውን አሳሳቢነት አስመልክቶ በምእራባውያን የኤምባሲ ዲፕሎማቶች የደህንነት አታቼዎች እና በወያኔ የደህንነት ባለስልጣናት ጋር ስብሰባ መቀመጣቸው ታውቋል።


ከወያኔ የደህንነት ባለስልጣናት ጋር ይደርሳሉ የሚባሉ ፍንዳታዎች ምዕራባውያን ላይ ያነታጠሩ በመሆኑ የሰጉት የሃያላኑ ዲፕሎማቶች ሁኔታው ከመከሰቱ በፊት ለመቆጣጠር ሲሉ አስፈላጊውን የዲፕሎማቲክ ሩጫ እያደረጉ መሆኑ ሲታወቅ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ከሆነ ምርጫ እየደረሰ ስለሆነ ተቃዋሚዎችንና ያልያዛቸውን ጠንካራ ሰዎች ለማፈስ ወያኔ የሚጠቀምበት ስልት ነው። ህዝቡን እያስፈራራ የውጭ አገር መንግስታትንም እንዲሁ አሸባሪ ለመዋጋት እያለ እራሱ የቀበራቸውን ፈንጂዎች ያስጮህብናል። የፈለገውንም ይገድላል። ስለዚህ ህዝቡ ነቅቶ መጠበቅ የግድ ይለዋል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/35459

Tuesday, October 14, 2014

በቅርቡ የተሰደደው ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹሩቤ ህይወቱ አለፈ

በቅርቡ የተሰደደው ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹሩቤ ህይወቱ አለፈ


milion shurbieየማራኪ መፅሔት ባለቤት እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር የነበረው ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹሩቤ በስደት በሚገኝበት ናይሮቢ ኬኒያ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በድንገት ህይወቱ ማለፉን ከማኀበራዊ ገፆች የተገኙ መረጃች እና ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ኢህአዴግ መራሹ የኢትዮጵያ መንግስት በጅምላ ያደረገውን የመፅሔቶች እና ጋዜጣ ክስ እና የበርካታ ጋዜጠኞችን እና ብሎገሮችን እስርን ፍርሃት ተከትሎ በቅርቡ ከተሰደዱ ጋዜጠኞች መካከል ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹሩቤ አንዱ ነበር፡፡
ጋዜጠኛው በስደት ኬኒያ ከሚገኝበት አንድ ናይሮቢ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቢቆይም ህይወቱን ማትረፍ እንዳልተቻለ ታውቋል፡፡ ጋዜጠኛው ከኢትዮጵያ ከተሰደደ ገና ሁለት ወር እንኳ እንዳልሞላው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ጋዜጠኛ ሚሊዮን የድርሰት ስራም እንዳለው ተጠቁሟል፡፡ አዲስ ሚዲያም ለጋዜጠኛ ሚሊዮን ፈጣሪ ነፍሱን በገነት እንዲያኖር፤ ለቤተሰቦቹ፣ለወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል፡፡
maraki magazine

Monday, October 13, 2014

Independent Ethiopian Journalist Temesgen Desalegn Arrested


Ethiopian journalist Temesgen Desalegn has been arrested by Ethiopian police today, October 13, 2014 for articles he wrote before 2013.
Temesgen was the editor in chief of the critical newspaper, Feteh, which was closed by government order. The Ethiopian government filed over 100 lawsuits against him, some of which he is still fighting. He has also been arrested briefly in 2013. He worked as the editor in chief of another critical magazine, Addis Times before it also
got closed by the government. 
Temesgen becomes raises the number of Ethiopian journalists and publishers charged and detained over 11 this year alone.
His next appointment is on October 27, 2014; the date he will be sentenced.
Source:: Debirhan

በሸኮ መዠንገር ታጣቂዎችና በፌደራል ፖሊሶች መካከል በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ከ50 በላይ የፌደራልና የመከላከያ አባላት ተገደሉ።

Today, October 13, 2014,
ጥቅምት ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ባለፈው ቅዳሜና እሁድ የፌደራል ፖሊሶችን ልዩ ሃይልንና መከላከያን ባቀፈው የመንግስት ጦርና፣ መሳሪያ በታጠቁ የብሄረሰቡ ተወላጆች መካከል በተደረገው ውጊያ ከ40 በላይ የፌደራል ፖሊስ አባላትና ከ10 ያላነሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ 4 ታጣቂ ሚሊሺያዎችና 3 የወረዳ ፖሊሶች ተገድለዋል። የሟቾቹ አስከሬን በሚዛን አማን ሆስፒታል እንዲገባ ከተደረገ በሁዋላ፣ ዘመድ ያላቸው ወደ ዘመዶቻቸው ሲሸኙ፣ የቀሪዎቹ የቀብር ስነስርዓት ደግሞ ሚዛን ውስጥ መፈጸሙን ለማወቅ ተችሎአል።
በአዲስ አበባ የፖሊስ ሆስፒታል ምንጮች እንደገለጹት ከሆነ ደግሞ በርካታ አስከሬን ወደ ሆስፒታሉ የገባ ሲሆን፣ በመዠንገሮች የተገደሉት የፌደራል ፖሊስ አባላት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የሚያመለክት ነው።

በሸኮና መዠንገር ታጣቂዎች በኩል የደረሰውን ጉዳት ለማወቅ ባይቻልም፣ በዛሬው እለት መንግስት ተጨማሪ ሃይል ወደ አካባቢው በመላክ ጥቃት መፈጸሙንና ብዙዎችን መግደሉን የአይን እማኞች ገልጸዋል።
ከብሄረሰቡ ውጭ ያሉ ሰፋሪ ነዋሪዎች በሚደርስባቸው ጥቃት የተነሳ ቀያቸውን እየለቀቁ ሲሆን፣ ብዙዎቹም ለከፋ ችግር ተዳርገዋል።
በፌደራል ፖሊሶች ላይ የደረሰውን ጉዳት በሚዛን አማን ሆስፒታልተገኝቶ የተመለከተ አንድ ወጣት፣ ሁኔታው አስከፊና አስፈሪ መሆኑን ገልጿል በሌላ በኩል በአካባቢው ያለው የኢሳት ወኪል እንደገለጸው 18 የፌደራል ፖሊስ አስከሬን መቁጠሩን ተናግሯል። መንግስት ታንኮችንና ከባድ መሳሪያዎችን ማጓጓዙን ገልጾ፣ የሸኮ መዠንገር ተወላጆች ሚዛን ከተማ ድረስ በመምጣት ነዋሪዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ የሚያሳስብ ወረቀት መበተናቸውንም ተናግሯል።በርካታ ቁጥር ያላቸው የተፈናቀሉ ኢትዮጵያን በሚዛን ከተማ ጎዳናዎች ላይ እንደሚታዩና እስካሁን እርዳታ ያደረገላቸው ድርጅት አለመኖሩንም ገልጿል።
መንግስት በጉዳዩ ላይ እስካሁን የሰጠው አስተያየት የለም። ከዚህ ቀደም በቴፒና ሜጤ በሚባሉት አካባቢዎች የነበረው ግጭት ወደ ጉራፈርዳ ወረዳ መሸጋገሩን እና የፌደራል ፖሊስ ወደ አካባቢው መሰማራቱን መዘገባችን ይታወሳል።
መስከረም አንድ በነበረው ግጭት መንግስት ከ 13 ያላነሱ ዜጎች መገደላቸውን ሲገልጽ፣ የአይን እማኞች የተገደሉትን ዜጎች ቁጥር ከ50 በላይ ያደርሱታል።

Abebe Gellaw’s Letter to U.S. President Barack Obama

October 13, 2014
by Abebe Gellaw
Note: Upon the invitation of the Democratic National Committee, I had another opportunity to attend an event with President Obama. He spoke about the opportunities and challenges that his administration is taking up at home and abroad. In the October 10 event held at The W Hotel in downtown San Francisco, I took this opportunity to hand the following letter to a White House aide, who promised to deliver it to the President. In any case, here it is in a form of an open letter to President Obama.
….
President Barack Obama
1600 Pennsylvania Ave NW,
Washington, DC 20500
Mr. President,
First and foremost, I would like to express my sincere appreciation to you for taking some bold steps to inspire the future leaders of Africa. The Mandela Washington Fellowship, which aims to bring 500 bright and visionary young African leaders to the White House and Capitol Hill annually for a unique experience and learning, is arguably one of the best initiatives that the government of the United States has ever taken.
I am sure many Africans support such an initiative because the future and hope of the African continent hinges upon new breed of visionary leaders that are willing to boldly take risks to lead Africa out of the darkness of brutal tyranny and corruption into the sunshine of freedom, dignity, justice and democracy.Obama at the W Hotel in downtown San Francisco
Some of these young dreamers and visionaries you are trying to inspire will certainly follow the footsteps of Martin Luther King Jr., Gandhi and Mandela. If African nations suffering under tyrannies are to get out of the quagmire of abject poverty, ignorance, corruption, abuse of power and the indignity they are suffering at the hands of its own rulers, a new breed of African leaders with selfless mindsets have to take the lead. However, we should also remember that countless young visionary Africans who could have joined the coveted fellowship cannot even apply because most are thrown in harsh jails, some are killed and many are tortured and abused because of their views and the beautiful dreams they cherish.
Mr. President, it would be disingenuous of me if I am remiss to raise the serious concerns that freedom fighters and activists like myself are expressing in the aftermath of the African Leadership Summit that you hosted last August. While the summit should be applauded as the first ever U.S.-Africa summit aimed at engaging African rulers, the list of guests was truly disturbing.
Just to mention a few among many, Teodoro Obiang of Equatorial Guinea, Gambia’s Yahya Jammeh, Cameroon’s Paul Biya, Jose Eduardo dos Santos of Angola even Ethiopia’s Hailemariam Desalegn, who is the front man for TPLF’s brutal regime, are among the worst human rights abusers in the continent that are shedding the blood of so many innocent people and terrorizing their own people to sustain their tyranny and corruption. Africa’s biggest obstacles to progress and change are its own abusive rulers. Without respect for human rights, progress and development has little meaning because it is not the aspiration of any nation to starve and die dispossessed of dignity in silence and fear.
Mr. President, it is true that some African countries are registering some progress. But in so many countries like Ethiopia, where crony capitalism is on the rise, the hyped up progress and development is driven by a greedy ethnocentric ruling elite. As you very well know, crony capitalism mainly benefits the privileged few at the detriment of the majority.
Mr. President, during your meeting with a delegation of Ethiopian officials that included Prime Minister Hailemariam Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom last month at the United Nations, you said: “Obviously we’ve been talking a lot about terrorism and the focus has been on ISIL, but in Somalia, we’ve seen al-Shabaab, an affiliate of al Qaeda, wreak havoc throughout that country. That’s an area where the cooperation and leadership on the part of Ethiopia is making a difference as we speak. And we want to thank them for that.” It is indeed a great honor for Ethiopia to get your administration’s commendation for its role in the global war on terror.
However, any careful reading of the annual State Department report on human rights reveals disturbing facts that maybe unintentionally overlooked. It is clear that the greatest threats on the safety and security of the ordinary people of Ethiopia do not come from al Qaeda or al-Shabaab. It comes from the very people who sat with you pretending to be committed to be fighting against terrorism. As a matter of fact, after the fall of the brutal military rule of Mengistu Hailemariam in 1991, it is a tragedy that another tyranny is under the TPLF is terrorizing Ethiopia for over two decades.
The TPLF regime has killed, maimed, tortured and jailed countless Ethiopians during its reign of terror. So many journalists, bloggers, activists, dissidents and freedom fighters are being jailed and tortured accused of fictitious terrorism charges. The award winning journalists Ekinder Nega, Reeyot Alemu, Wubishet Taye, the young Zone9 bloggers, leaders of Muslim rights movement, activists and dissidents like Andargachew Tsege, Andualema Arage, Bekele Gerba, Olbana Lelisa and countless others have been labeled terrorists. They are languishing in rat-infested jails abused, tortured and brutalized. Such a cowardly attack against innocent civilians for speaking out against tyranny is nothing but terrorism.
President Obama, please allow me to quote just two paragraph from the 2013 U.S. State Department Human Rights Report on Ethiopia: “The most significant human rights problems included: restrictions on freedom of expression and association, including through arrests; detention; politically motivated trials; harassment; and intimidation of opposition members and journalists, as well as continued restrictions on print media. On August 8, during Eid al-Fitr celebrations, security forces temporarily detained more than one thousand persons in Addis Ababa. The government continued restrictions on activities of civil society and nongovernmental organizations (NGOs) imposed by the Charities and Societies Proclamation (the CSO law).”
“Other human rights problems included arbitrary killings; allegations of torture, beating, abuse, and mistreatment of detainees by security forces;reports of harsh and, at times, life-threatening prison conditions; arbitrary arrest and detention; detention without charge and lengthy pretrial detention; a weak, overburdened judiciary subject to political influence; infringement on citizens’ privacy rights, including illegal searches; allegations of abuses in the implementation of the government’s “villagization” program; restrictions on academic freedom; restrictions on freedom of assembly, association, and movement; alleged interference in religious affairs; limits on citizens’ ability to change their government; police, administrative, and judicial corruption; violence and societal discrimination against women and abuse of children; female genital mutilation/cutting (FGM/C); trafficking in persons; societal discrimination against persons with disabilities; clashes between ethnic minorities; discrimination against persons based on their sexual orientation and against persons with HIV/AIDS; limits on worker rights; forced labor; and child labor, including forced child labor. Impunity was a problem. The government, with some reported exceptions, usually did not take steps to prosecute or otherwise punish officials who committed abuses other than corruption.”
Mr. President, I hope you agree with me that the disturbing testimony from the State Department is as bleak as a CIA report on al-Qaeda. It should be noted here that the Tigray People’s Liberation Front was also blacklisted in the Global Terrorism Database of the U.S. Department of Homeland Security before it came to power. Terrorist groups, whether they operate as a government or a band of pirates, have similar objectives and aspirations. They try to cause great fear and impose their will upon others through killings, massacres, tortures, kidnappings and all sort of inhuman tactics.
In the aftermath of the 2005 brutal crackdown, U.S. Senator Patrick Leahy had said, in a statement, “Ethiopia has been an ally of the United States in combating international terrorism, yet it is using similar tactics against its own people…The government’s heavy handed tactics to steal the election and persecute those who sought to play by the rules of democracy, should be universally condemned.”
Mr. President, so many Ethiopians appreciate your effort to help Ethiopia. But the United States should not provide unconditional funds to the tyrants in power that are terrorizing the oppressed people of Ethiopia. The United States should not also lose its unique place as the beacon of hope and freedom. It needs to live up to its core values and creeds. If the United States needs credible allies against terrorism, it has to look into the records of questionable allies and press them to clean their own house first before fighting other terrorists.
Mr. President, as you said: “We lose ourselves when we compromise the very ideals that we fight to defend. And we honor those ideals by upholding them not when it’s easy, but when it is hard.”
Ordinary people like me will continue to make every effort to stick out reminders and notes so that the government of the United States continues to uphold the foundational values and ideals that have made this country truly great and admirable. I do hope that eventually we will get noticed and our voices will be heard.
We need Freedom! Justice! Dignity! Democracy! and Equality.
Most respectfully,
Abebe Gellaw
Global Alliance for the Rights of Ethiopians

Sunday, October 12, 2014

የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ በደህንነት ሰዎች ተደበደቡ

October 12,2014
ፍኖተ ነፃነት
10710933_711118828973054_6184937440487717547_nየአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የሰሜን ቀጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ አዕምሮ አወቀ ሐሙስ ዕለት ከሥራ ወደ ቤታቸው ሲጓዙ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡ እንደ አቶ አዕምሮ ገለፃ ይህ ድርጊት በየጊዜው እንደሚከሰትና በሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት እንቅስቃሴ በደሴ ከተማ በመኪና ለማፈን በተደረገው ግብግብ መኪና ውስጥ አስገብተው እንደተደበደቡ ራሳቸውን ለመከላከል በሚታገሉበት ወቅትም ጋቢና የተቀመጠውን ሹፌር መኪናውን ለማስነሳት ቁልፍ እንደያዘ እጁን ሲረግጡት በመጎዳቱ፣ ሁለቱ ከኋላ የያዟቸውን ደህንነቶች ለመከላከል ባደረጉት ግብ ግብ ስላየሉባቸው ገፍትረው ከመኪናው እንደጣሉዋቸውና ወደ አዲስ አበባ ከመጡም በኋላ ወንድማችንን ደብድበሃል የትም አታመልጥም በሚል ለገሃር አካባቢ በቡድን ድብደባ እንደፈጸሙባቸው ገልጸዋል፡፡
 በተመሳሳይ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ከሰሜን የሚመጡ የፓርቲው አባሎችን ለመቀበል ዝግጅት በሚያደርጉበት ታህሳስ 17/2006 ዓ.ም ቤታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተሰብሮ ንብረቱ በሙሉ ከቤት ተጭኖ ተወስዷል፡፡ ሐሙስ ዕለትም ከሥራ ወጥተው በትራንስፖርት ወደ ቤታቸው በሚሄዱበት ወቅት አየር ጤና አካባቢ ከአውቶቡስ ሲወርዱ ሁለት ደህንነቶች ግራና ቀኝ እጃቸውን በመያዝ እንዳይንቀሳቀሱ ካደረጉዋቸው በኋላ ሦስተኛው ደህንነት በድንጋይ ከጉልበታቸው በታች ደጋግሞ በመምታት ቀኝ እግራቸው ላይ ጉዳት አድርሰው ሦስቱም ከአካባቢው እንደተሰወሩ ገልጸዋል፡፡ ይህ ህገ ወጥ ድርጊት በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እንዲመጣ መታገሌን እንዳቆም እንደማያደርገኝ ሊያውቁት ይገባል በማለት ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ይፈርሳል? ይህን ማኅበር ሚገዳደሩት እነማን ናቸው? (በካሌብ ብርሃኑ)

ማኅበረ ቅዱሳን ይፈርሳል? ይህን ማኅበር ሚገዳደሩት እነማን ናቸው? (በካሌብ ብርሃኑ)


ሰሞኑን በኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ክርስቲያኖች መካከል የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖ የሰነበተው የማህበረ ቅዱሳን ጉዳይ ነው። ፓትርያርኩ አቡነ ማትያስ የማህበረ ቅዱሳን ጉዳይን ለቅዱስ ሲኖዶስ አቅርበው ተነጋግረውበት ነበር። ሆኖም ቅዱስ ሲኖዶሱ በማህበረ ቅዱሳኑ ላይ ጠንካራ ተቃውሞ አላቀረበም፤ ወይም እርምጃ አልወሰደም። በመሆኑም ፓትርያርኩ እታች ወርደው የቤተ ክርስቲያኑ ሌሎች አመራሮች ጋር ስብሰባ አደረጉ። የስብሰባው አጀንዳ በቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር ውስጥ ስላለው የመልካም አስተዳደር እጦት ነበር። ሆኖም ስብሰባው ሲጀመር መስመሩን እየለቀቀ ሁሉም በማህበረ ቅዱሳን ላይ የጭቃ ጅራፍ ያወርድበት ጀመር።
በስብሰባው ላይ የተገኙት ሰዎች ማህበረ ቅዱሳንን ከአሸባሪ አካላት ጋር በማያያዝ ሃሳባቸውን ሲገልጹ ሰምተናል። የማህበረ ቅዱሳን የባንክ አካውንት እንዲዘጋም የጠየቁ ነበሩ። እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ልዩነት ካለ በልዩነት ዙሪያ መነጋገር ሲቻል፤ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን አባላት የጽናት መሰረት የሆነውን ማህበረ ቅዱሳንን “አሸባሪ” ብሎ ስም መስጠት በጣም አሳፋሪ እና አግባብ ያልሆነ ተግባር ነው። አሸባሪ የምትለዋን ቅጽል ይዘው ማህበሩን ሲያብጠለጥሉት ቆዩና በሚቀጥሉት ቀናት “የማህበረ ቅዱሳን የባንክ አካውንት ተዘጋ” የሚለውን ዜና ሰማን። እስካሁን ያልሰማነው “የማህበረ ቅዱሳን አመራሮች በአሸባሪነት ታሰሩ” የሚለውን ነው። ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ግን የመታሰራቸውን ዜና የምንሰማበት ግዜ እሩቅ አይሆንም።
እንግዲህ ሰሞኑን በዚህ አሳዛኝ እና አስደማሚ ዜና እየሰማን ቆየን። ምናልባት ማህበረ ቅዱሳን በዚህ ጉዳይ መግለጫ ይሰጥ እንደሆን ብለንም ጠበቅን። ምንም የሰማነው ነገር የለም። ሆኖም ስለማህበረ ቅዱሳን የሰሞኑ ጉዳይ አጸፋዊ መልስ ባይሆንም ማብራሪያ የተሰጠበት አንድ ጽሁፍ ደረሰን። የጽሁፉ አቅራቢ ካሌብ ብርሃኑ ይባላል። ግላዊ እይታውን አቅርቧል። እናም ይህ በትንሹም ቢሆን የማናውቀውን ያሳውቀናልና ጽሁፉን ልናጋራቹህ ወደድን። ከዚህ በታች ያንብብቡት።
ማኅበረ ቅዱሳን ይፈርሳል? ይህን ማኅበር ሚገዳደሩት እነማን ናቸው? በካሌብ ብርሃኑ (ግላዊ እይታ)
የብዙ ወንድሞች እና እህቶች ጥያቄ ነው፤ እስኪ የኔን አስተያየት ላቅርብ፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ማለት ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንደተነገረው (አንዳንዶች ሰምተው እንዳልሰሙ፤ አንብበው እንዳላነበቡ፤ አውቆ የተኛ ቢቀሰቅሱት አይሰማም ብለው ተርተው አልሰማንም አሉ እንጂ) የቅዱሳን ስብስብ ሳይሆን ቅዱሳን ተጋድሎአቸው የሚዘከርበት፤ የመንፈስ ልጆቻቸውም አሰረ ፍኖታቸውን የሚከተሉበት የአገልግሎት ማኅበር ነው፡፡ ቢሆንም ቅሉ ብዙ ሰዎች እዚህ ማኅበር ላይ ቂማቸው እና ጥላቻቸው እየጨመረ መሄዱ የእለት ተእለት ተግባራቸው ለአንዳንዶችም መተዳደሪያ ስራቸው ሆኗል ፡፡ እኔ በግሌ ማኅበሩን ለምን ጠሉት አልልም መውደድና መጥላት የነሱ ነፃ ፈቃድ ነው፤ (እስከማውቀውም ድረስ ማኅበሩ ለመወደድ ብሎ ሲሰራ አላጋጠመኝም)፡፡ በመሆኑም የነዚህ ሰዎች ጥላቻ ማኅበሩን ያፈርሰዋል ወይ ወደሚለው የብዙዎች ጥያቄ ላምራ፤ ይህን ጥያቄ ለመመለስ መጀመሪያ ማኅበሩ ምንድነው ፤ የመጨረሻ ግቡስ የሚሉትን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ምንድን ነው?
ይህን ለመመለስ ከተመሰረተ ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየሰራ የለውን ሥራ በተጨባጭ መረጃ መገምገም ቀላሉ መፍትሔ ነው፡፡ በብዙ ቦታዎች እንደተገለፀው ማኅበሩ ሲቋቋም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኝ ተማሪዎችን በመንፈሳዊ ህይወት አንፆ ማሳደግ በዓለማዊውም ትምህርታቸው ጠንካራ ኦርቶዶክሶችን ማፍራት በዚህም በስነ ምግባር የታነፁ ዜጎችን ለኢትዮጵያና ለኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ማበርከት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የተማሩ ሰዎች ስብስብ እንደመሆኑም መጠን ቤተ-ክርስቲያኗ በተለይም ገዳማቶቿ የእውቀት እና የነገ ቤተ-ክርስቲያን መሪዎች መፍለቂያ እንደመሆናቸው መጠን ከ እርዳታ እና ከ ጥገኝነት ተላቀው እራሳቸውን የሚችሉባቸውን ፕሮጀክቶች በመንደፍ እና ተግባራዊ በማድረግ እንዲሁም የተዘጉና የተዳከሙ የ አብነት ትምህርት ቤቶችን በማጠናገር እና በማስከፈት መምህራንና ተማሪዎችንም ስፓንሰር በማድረግ ለተፈለገው የቤተ-ክርስቲያን አገልግሎት እንዲበቁ የማድረግን ስራ መስራት ነው፡፡ ማኅበሩ ሲቋቋም እንደ ሌሎች ማኅበራት በሰዎች ስምምነት ብቻ ሳይሆን በቤተ-ክርስቲያኗን ከአምላክ ቀጥሎ የመጨረሻ አዛዥ በሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ መተዳደሪያ ደንብ እና ቡራኬ የተሠጠው፤ ለዚህ አገልግሎቱም ከቤተ-ክርስቲያኗ መዋቅር ስር ሆኖ የሚያገለግል የ አገልጋዮች ማኅበር ነው፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ግን ይህ ከላይ የተገለፀው ብቻ አይደለም ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ እንደመሆኑ አንፃር በብዙ አባቶች እንዲሁም አገልግሎቱን ቀና እንነት በተገነዘቡ ሰዎች “የቤተ-ክርስቲያን የችግር ጊዜ ልጅ” የሚል ስያሜም ተሰጥቶታል፡፡ ይህ የተባለበት ምክንያት ደሞ አጽራረ ቤተ-ክርስቲያኖች የመነኩሴ ቆብ ለብሰው ህዝቡን ሊያወናብዱ “ቤተ-ክርስቲያኗ አርጅታለች እናድሳታለን” እያሉ በየአዳራሹ በሚበጠብጡበት ጊዜ ተከታትሎ ጉዳዩን ለቤተ-ክርስቲያኗ የበላይ አካላት (ቅዱስ ሴኖዶስ) በማስረጃ በማቅረብ አባቶች ውሳኔ እንዲሰጡ በማድረጉ እና አለማዊውን ትምህርት በከፍተኛ የትምህርት ደረጃ ያጠናቀቁ ክህናት ሙህራንን ለ ቤተ ክርስቲያኗ አገልግሎት በማቅረቡ ነው፡፡ ይህ ደሞ ኢንጅነሮቻችን በነፃ ዲዛይን በሚያደርጓቸው ቤተ-ክርስቲያኖች፤ ምሁራኖቻችን በሚያቀርቧቸው የጥናት እና ምርምር ስራዎች ውስጥ የሚታይ መሬት ላይ የወረደ እውነት ነው፡፡
በአሁኑ ስዓት ማኅበረ ቅዱሳን ማለት ይህ ማለት ብቻ አይደለም ምክንያቱ ደግሞ ማኅበረ ቅዱሳን ከአገልጋዮች ስብስብነት ወደ እሳቤ (ideology) አዊነት ስለተሸጋገረ ነው፡፡
ይህን ስል ምን ለማለት ፈልጌ እንደሆነ በምሳሌ ልግለፅ ፡-
ከጥቂት ወራቶች በፊት እንዲህ ሆነ በአውሮፓ ሀገር የምትኖር እህት በቤተ-ክርስቲያን ውስጥ ከኦርቶዶክሳዊ ስርአት ውጪ የሆነ ስራ ሲሰራ አይታ “ለምንድነው እንደዚህ ሚሰራው ከ አባቶች ያልወረስነው በመፅሐፍም ያልተፃፈ ከ ቤተ-ክርስቲያናችንም ትውፊት ውጪ የሆነ ሥራ ለምን ይሰራል ብላ ትጠይቃለች” በዚህ ሰዓት ይህቺ እህት አንቺ እማ ማኅበረ ቅዱሳን ነሽ ሚል ታፔላ ይለጥፉባታል ፤ ማኅበሩ ከነመፈጠሩ የማታውቀው እህት ይህ የተሰደብኩበት ማኅበር ማን ነው ብላ ማፈላለግ ትጀምራለች በመጨረሻም ወደ ኢትዮጵያ በምትመጣበት ወቅት ብዙ ጥናቶችን በማኅበሩ ላይ ካደረገች በኋላ ወደ ስራ አስፈፃሚ ቢሮ ቀርባ የታማሁባችሁ እናንተ የቤተ-ክርስቲያን ተስፋ ናችሁ በማለት ቤተ-ክርስቲያን ሥርዓት ሚፈፀምባቸውን መንገዶች እንድ ማሳያ ፕሮጀክት በመንደፍ የፕሮጀክቱን ማስፈፀሚያም አስተዋፅኦ በማድረግ ወደ አገልግሎቱ ገባች፡፡ ከዚህ ታሪክ የምንረዳው ነገር ስርዓት ሲጣስ የሚጠይቅ ፤ ስለቤተ-ክርስቲያን ፍቅር ልቡ የሚነድ እና ሲለሚፈፀምባት በደል የሚታመም መፍትሄም የሚፈልግ ሰው እሱ ማኅበረ ቅዱሳናዊ ነው ወደሚል መደምደሚያ እየተዞረ መሆኑን ማሳየት ነው ይህ ደሞ በማኅበሩ አባላቶች የተገለፀ ሳይሆን፤ በግልባጩ ቤተ-ክርስቲያኒቷን ለማውደም ከሚንቀሳቀሱ አካላት የመጣ እውነታ ነው፡፡
የማኅበሩ የመጨረሻ ግብ፡-
የማኅበሩ የመጨረሻ ግብ ምንድነው? ወደሚለው ጥያቄ እንዙር፤ ማኅበሩ በግልፅ እንዳስቀመጠው “ቤተ-ክርስቲያን የመሪነት ቦታዋን ማስመለስ” ነው፡፡ ይህ ምን ማለት ነው ብዙ ሰዎች ይህን ሲሰሙ ሊደናገጡ ይችላሉ ፤ አንዳንዶችም በስልጣናቸው የተመጣባቸው ሰለሚመስላቸው ማኅበሩን ለማጥፋት ጉድጓድ ሲቆፍሩ ይታያሉ (አጥልቃችሁ አትቆፍሩት ….) ፤ ቤተ-ክርስቲያንን የመሪነት ቦታዋን ማስመለስ ሲባል ምን ማለት እንደሆነ ባጭሩ ላቅርብ፡፡
ቤተ-ክርስቲያን በቀደምት ዘመናት የነበራት ቦታ አለ ይህም የተሰሚነት ፤ አገርን የማገልገል ፤ “በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀመዛሙርቴ አድርጓቸው” የሚለውን የአምላኳን ትእዛዝ መፈፀም ፤ በልማትና እርዳታ ከፍተኛ ቦታ ላይ መድረስ ወደምትችልበት ቦታ ማድረስ መቻል ማለት ነው፡፡
ታዲያ ይህን ማኅበር ሚገዳደሩት እነማን ናቸው?
1. መንግሥት ፡-
መንግሥት እንደ አስተዳዳሪነቱ ሁሉም ነገሮች (በተለይም የምሁራን ስብስብ) ያስፈራዋል በተለይ ደግሞ ብሔር ተኮር ለሆነ የገዢ ስርዓት ስለ አንድነት የምታስተምር ቤተ-ክርስቲያን ፈተናው ነች፡፡ ለዚህም ማሳያው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእስራኤላውያን ዘር ቢመጣም በፊቱ ቀለም ሳይሆን ባፈሰሰው ደም አለምን አድኗል፡፡ መልካችን ቢለያይም ደማችን ግን አንድ ነው ብላ ማስተማሯ መንግስት ከ በረሃ ጀምሮ ጥርሱ ውስጥ እንድትገባ አደርጓታል፡፡ ይህን አስተምህሮቷን ለማዳከም በሚሰራቸው ስራዎች ውስጥ ደሞ ቤተ-ክርስቲያኒቷን ሊያጠናክሩ የሚችሉ አካላትን ማጥፋት ካልተቻለ ማዳከም ሁነኛ መፍትሔው ነው፡፡
2. አፅራረ ቤተ-ክርስቲያናት፡-
እነዚህ አካላት ደሞ ቤተ-ክርስቲያኗን ለማፍረስ ምእመናኖቿንም ለመረከብ ብዙ የሚለፉ የእምነት ድርጅቶች ናቸው፡፡ በተለይም በቤተ-ክርስቲያኗ መዋቅር ውስጥ በመግባት ተሐድሶን እናደርጋለን የሚሉ ቅጥር ፕሮቴስታንቶች ሲሆኑ በኦርቶዶክስ ማልያ ለሌላ ቡድን ሚጫወቱ ናቸው፡፡ እነዚህ አካላት የሉም እያሉ በየቦታው ቢያስነግሩም በየእጆቻችን ያሉት መረጃዎች ይህን አያመላክቱም፡፡ ይባስ ብለው እነዚህ ሰዎች መፃህፍትን እና ቪዲዮችን በመልቀቅ አለን እናድሳታለንም እያሉ ሲፎክሩ ይታያሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች እንደነበራቸው እቅድ በ ሚሊኒየሙ (2000 ዓ.ም) ሙሉ በሙሉ ቤተ ክርስቲያኗን እንረከባታለን ብለው እቅድ ቢያወጡም ሊሳካላቸው አልቻለም ፡፡የዚህን ምክንያትም ሲናገሩ ማኅበረ ቅዱሳን የሚባል የወጣት ሙህራኖች ስብስብ እንቅፋት እንደሆነባቸው ያስረዳሉ በመሆኑም በሚቀጥለው ስትራቴጂያቸው በቻሉት አቅም ቤተ-ክርስቲያኗን ለመረከብ ማኅበሩን ማጥፋት ካልቻሉ ደግሞ ማዳከም ሁነኛ መፍትሔ ነው፡፡
3. ጥቅማቸው የተነካ የቤተ-ክርስቲያኒቷ አካላት ፡-
እነዚህ አካላት ቤተ-ክርስቲያኒቷ ላይ ኑራቸውን ጥገኛ ያደረጉ ነገር ግን ከሚገባቸው በላይ የቤተ-ክርስቲያኒቷን ንብረት ለመቀራመት የሚተጉ ፤ ምንኩስናን እና ቅስናን ክፍት የስሥራ ማስታወቂያ ያደረጉ የቤተ-ክርስቲያኗ አካላት ናቸው፡፡ እነዚህ አካላት ከ ሰበካ ጉባኤ አባልነት እስከ ቤተ-ክርስቲያኗ ከፍተኛ የስራ አመራር ደረስ የተሰገሰጉ ቡድኖች ሲሆኑ ፤ ማኅበሩ እያደረገ ያለው አገልግሎት የነሱን ጥቅም የነካ (የሚነካ) የመሰላቸው (የነካባቸው) አካላት ናቸው፡፡ ለዚህም ነው የማኅበሩን አገልጋዮች ባዩ ቁጥር “ባለ ድግሪው ሊቀድስ መጣ” እያሉ ሚጨነቁት ምክንያቱ ደሞ የማኅበሩ አገልግሎት መርህ ቤተ-ክርስቲያንን በ ገንዘብ በጉልበት እና በእውቀት ማገልገል በመሆኑ ሚሰራቸው እያንዳንዳቸው አገልግሎቶች ለቤተ-ክርስቲያን በነፃ ሚደረጉ ሲሆን እነዚህ አካላት ደሞ በቤተ-ክርስቲያኗ ተከፋይ (ሊያውም ከሚገባቸው በላይ) በመሆናቸው ነው፡፡ ተከፋይ ስል በቤተ-ክርስቲያን በ አገልግሎት ለሚሳተፉ መደበኛ አገልጋዮች ሚከፈላቸውን ደሞዝተኞች አለመሆኑ ይተወቅልኝ፡፡ ይልቅስ አንዲት ፕሮጀክት ለመተግበር የ አስር ፕሮጀክት ብር የሚበሉትን ለማጠየቅ ነው፡፡ እናም እነዚህ አካላት ተደላድለው የቤተ-ክርስቲያኒቷን ሃብት ለመብላት ማኅበሩን ማጥፋት ካልቻሉ ደግሞ ማዳከም ሁነኛ መፍትሔአቸው ነው፡፡
4. ማኅበሩን ባለማወቅ እንቅፋት የሚሆኑ፡-
እነዚህ አካላት ስለማኅበሩ ምንም ባለማወቅ ወይም ከላይ የተገለፁትን አካላት እንደ መረጃ ምንጭ በመውስድ ለማኅበሩ እንቅፋት የሚሆኑ አካላት ናቸው፤ በዚህ ምክንያትም አንዳንዶች ማኅበሩን የተሐድሶ መነሻና መድረሻ አድርገው የሚያስቡ ሆነዋል፡፡ ሌሎች ደግሞ ማኅበሩ ከ ሰንበት ት/ቤቶች ጋር ፉክክር የገባ የሰንበት ት/ቤቶችን ለመብለጥ (ለማዘዝ) የተቋቋመ እየመሰላቸው ማኅበሩን ለመጣል ብዙ ሲለፉ እናያቸዋለን፡፡ እነዚህ ወገኖች ሁላችንም አንዲት ቤተ-ክርስቲያን ለመገንባት የምንጥር መሆናችንን አልተረዱም፡፡ ይልቅም ማኅበሩ ከብዙ ሰንበት ት/ቤቶች ጋር በጋራ ስለሚሰራቸው ስራዎችም እንዲሁም ሰንበት ት/ቤቶችን ለማጠናከር የሚሰራውን ስራ አልተገነዘቡም፡፡ የዚህም ማሳያው የሰንበት ት/ቤቶችን መጠናከር ሲመለከቱ “እሰይ ከማኅበረ ቅዱሳን እየበለጡ ነው” እያሉ በየመድረኩ የሚሰጡት ያላዋቂ አስተያየት ነው፡፡
ይህን ያህል ማኅበሩን ሊያጠፉት (በማወቅም ሆነ ባለማወቅ) ስለ ሚጥሩት አካላት ከገለፅን እውን ማኅበሩን ማጥፋት ይችላሉ ወይ? ወደሚለው የመጨረሻ ጉዳይ እንሂድ፡፡
ማኅበሩን ሊያጠፉት አይችሉም!!!፡፡ እንደምን እንደማይችሉ በትንሹ ልግለፅ ፤ ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርኩት ማኅበሩ አሁን የአገልጋዮች ስብስብ ብቻ ከመሆን ዘሎ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤ (ideology) ወደ መሆን ተሻግሯል፡፡ እነዚህ ሰዎች ማኅበረ ቅዱሳናውያን ብለው ሚያስቡት በአባልነት የተመዘገቡትን ከ 60,000 በላይ አባላት ሊሆን ይችል ይሆናል ነገር ግን አሁን ከዛም አልፏል፤ ማኅበረ ቅዱሳናዊነት በያንዳንዱ ለቤተ-ክርስቲያን ይገባኛል በሚል ኦርቶዶክሳዊ ውስጥ ያለ አስተሳሰብ ነው፡፡ ቤተ-ክርስቲያኔን ባለኝ ነገር ሁሉ ላገልግል በሚል ኦርቶዶክሳዊ ውስጥ ያለ አስተሳሰብ ነው፡፡ ይህን ደሞ ተቋሙን በማፍረስ ማጥፋት የሚቻል አይደለም፤ ብዙዎች ማኅበሩ አሁን ካለበት የአደረጃጀት ስርአት ቢበተን የልባቸው የሚሳካ ይመስላቸዋል፡፡ በጣም ትልቅ ስህተት ነው ምክንያቱም አሁን እንደሚታየው ማኅበሩ ላይ ያሉት አባላት በአንድ መዋቅር ስር የተሰበሰቡ ናቸው ይህ ደሞ ተወደደም ተጠላም ለነዚህ አገልጋዮች የሚያስቀምጥባቸው ድንበር (limitation) አለ፤ ይህን መዋቅር መበተን ግን እነዛን ሰዎች ያለ ምንም ድንበር አገልግሎት ላይ እንዲሳተፉ የሚያስችል ሌላ ትልቅ የአገልግሎት በር መክፈት ነው፤ ይህ ደሞ እያንዳንዱ ኦርቶዶክሳዊ ወደ ቤተ-ክርስቲያን እንዲመለስ እና በትጋት እንዲያገለግል የሚያደርግ ጥይት መተኮስ ነው፡፡ በዚህ ሰዓት ሊፈፀም የሚችለው አንድ እና አንድ ነገር ብቻ ነው እያንዳንዱ ሰንበት ት/ቤት እና ሰበካ ጉባኤ ማኅበረ ቅዱሳናዊ እሳቤን ወደመያዝ ይዞራል ያኔ “በተንን” የሚሉት መዋቅር ሺ ጊዜ ጠንክሮ እና አብቦ ይመጣል፡፡